Tuesday, June 30, 2015

ግብረሰዶም እና መፅሃፍ ቅዱስ (ከTeaching of EOTC የፌስቡክ ገፅ የተወሰደ)

“ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮ ሆኑ” ሮሜ. 1÷22
በዚህ ዘመን ግብረ ሰዶማዊነት እንደ ጥሩ ነገር እየታየ በመምጣቱ ጠዋትና ማታ በተለያዩ ማስ ሚዲያዎች፣ ድረ ገጾች፣ ፊልሞች፣ ጋዜጦች እና መጽሔቶች ይቀነቀናል፤ ይሰበካልም፡፡ አንዳንዶችም ከሰው ልጅ ሥልጣኔ ጋር አብሮ የመጣ አድርገው ሲመለከቱት እና ሲያናፍሱት እናስተውላለን፡፡
በሰለጠነው ዓለም በወንድና በወንድ መካከል ያለው የግብረ ሰዶማዊ ግንኙነት (Gays) በሴትና በሴት መካከል ያለው የግብረ ሰዶማዊ ግንኙነት (Lesbians) እንደ ጥሩ ነገር እየታየ መምጣቱ ብቻ ሳይሆን ሕጋዊነት እያገኘ መጥቷል፡፡ በርካታ ሀገሮች የወንድ ለወንድ እና የሴት ለሴት ጋብቻን ከፈቀዱ ሰንብተዋል፤ በሒደት ላይ ያሉም ብዙ ናቸው፡፡ በአሜሪካና በአውሮፓ የሚገኙ አንዳንድ የእምነት ተቋማትም/ፕሮቴስታንት እና ካቶሊክ ድርጅቶች/ ከመሪዎቻቸው ጀምሮ በዚህ ግብረ ሰዶማዊ ግብር ስለቆሸሹ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ግብረ ሰዶማዊነትን ደግፈው ሲሰብኲ እንዲሁም ወንድ ለወንድ ሲያጋቡ ታዝበናል፡፡ ይህ አስደንጋጭ እና አሳፋሪ ክስተት ብዙዎቻችንን ሊያስደነግጠን ቢችልም መጽሐፍ ቅዱስ ግብረ ሰዶማዊነት ዛሬ የተጀመረ ክፉ ግብር ሳይሆን ጥንትም የነበረ ብዙዎችን ያረከሰ ነውር እና አስጸያፊ ተግባር መሆኑን ይመሰክራል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ፡- የመጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያ መጽሐፍ በሆነው በኦሪት ዘፍጥረት መጽሐፍ ስለ ግብረ ሰዶማዊነት ይናገራል፡፡ የሰዶምና የገሞራ ሰዎች ግብረ ሰዶማውያን ነበሩ፡፡ ሰዶምና ገሞራ በዮርዳኖስ ሸለቆ የተቆረቆሩ ከተሞች ነበሩ፡፡ በእነዚህ ሁለት ከተሞች ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ግብረ ሰዶማውያን ማለትም ወንድ ከወንድ፣ ሴት ከሴት ጋር ዝሙት የሚያደርጒ ይህ ኃጢአትም በእነርሱ ይበዛ ስለነበር ስያሜው የቦታውን ስም በመያዝ ግብረ ሰዶም ተባለ፡፡ በዘመናት ሁሉ ይህን ኃጢአት የሚሠሩ መጠሪያ ሆኖ አገለገለ፡፡ ዛሬም በግብር የሚመስሉአቸው ሰዎች ግብረ ሰዶማዊ ወይም ሰዶማውያን እየተባሉ ይጠሩበታል፡፡ የሰዶምና የገሞራ ሰዎች ወንድ ከወንድ፣ ሴት ከሴት ጋር የሚፈጽሙት ዝሙት አጸያፊ ስለነበር እግዚአብሔር ሊያጠፋቸው ወሰነ፡፡ (ዘፍ. 18÷20፣ ዘፍ.19÷5-9)፡፡ ሁለት መላእክትን ወደ ሰዶም ላከ፡፡ ሁለቱ መላእ ክት የእግዚአብሔር ሰው እና ከሰዶማዊነት ግብር ንጹሕ የነበረውን ሎጥን ከከተማው እንዲወጡ ካደረጉ በኋላ እግዚአብሔር ሰዶምንና ገሞራን በእሳትና በዲን አጠፋ፡፡ (ዘፍ.19÷10-26) ሰዶምና ገሞራ አሁን በጨው ባሕር እንደተሸፈኑ የሥነ ምድር ተመራማሪዎች ይናገራሉ፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ ሰዶምና ገሞራ የክፋት ሁሉ የፍርድም ምሳሌ በመሆን ተጠቅሰዋል፡፡ (ኢሳ. 1÷9-10፣ ኢሳ. 3÷9፣ ኤር. 23÷14፣ ሰ.ኤ.4÷6፡፣ ሕዝ. 16፡46፣ ማቴ.10÷15፣ ራእ. 11÷8)
ሰዶማዊነት ነውር ነው፡-
መጽሐፍ ቅዱስ ግብረ ሰዶማዊነት ነውር እና አጸያፊ እንደሆነ ይመሰክራል፡፡ ነውር የሆነበትም ምክንያት ይህ ነው፡፡
ሀ. እግዚአብሔር የመሠረተውን የጋብቻ ሥርዓት ማለትም አንድ ወንድ ለአንዲት ሴት የሚለውን ሕግ የሚያፈርስ በመሆኑ፤
ለ. በሁለት ተቃራኒ ጾታ ማለትም በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል የሚደረገውን ተፈጥሮአዊ የግብረ ሥጋ ግንኙነት/መሳሳብ/ የሚያቆሽሽ አዲስ ልምድ ስለሆነ፤
ሐ. የሰው ልጅ ዘሩን የመተካት ከፊጣሪ የተሰጠውን መብቱን የሚገፋ (የሚያሳጣ) ተግባር በመሆኑ፤
መ. ሰዶማዊነት በአንድ ወንድ ወይም በአንዲት ሴት ብቻ የሚቆም ግብር ስላልሆነ፤ ወንዱ ብዙ ወንዶችን ሴቷ ብዙ ሴቶችን ሲለምዱ ለተለያዩ በሸታዎች ስለሚያጋልጥ፤
ሠ. ሰዎች ስለ ፍቅር ትክክለኛ ሥእል እንዳይኖራቸው እና በስሜት የሚነዱ ራስ ወዳዶች እና ሓላፊነት የማይሰማቸው ዜጎችን ስለሚፈጥር፤
ረ. የተለያዩ አካላዊ፣ ሥነ ልቡናዊ እና መንፈሳዊ ክስተቶችን ስለሚያስከትል በእግዚአብሔር የተናቀ እንዲሁም የተጠላ ግብር ነው፡፡ከተፈጥሮ ሥርዓትና ሕግ ውጪ በመሆኑ በኅብረተሰቡም ዘንድ ተቀባይነት የሌለው ማኅበራዊ መገለልን የሚያስከትል ክፉ ተግባር ነው፡፡ይህ ክፉ ግብር ወንድ ከወንድ ሴት ከሴት ጋር ብቻ ሳይሆን ከእንስሳትም ጋር ግንኙነትእንዲፈጽሙ በር የሚከፍት ነውረኛ ሕይወት ነው፡፡
“ማናቸውም ሰው ከሴት ጋር እንደሚተኛ ከወንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድርገዋል፤ ፈጽመው ይገደሉ፤ ደማቸው በላያቸው ነው፡፡” (ዘሌ. 30÷13)
“የሰዶም ሰዎች ግን ክፉዎችና በእግዚአብሔር ፊት እጅግ ኃጢአተኞች ነበሩ፡፡” (ዘፍ. 13÷13)
“እንዲሁም እንደ እነርሱ ዝሙትን ያደረጒና ሌላን ሥጋ የተከተሉ ሰዶምና ገሞራ በዙሪያቸው የነበሩ ከተማዎችም በዘላለም እሳት እየተቀጡ ምሳሌ ሆነዋል፡፡” (ይሁዳ. ቁ. 7)
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በሮሜና በቆሮንቶስ መልእክቱ ግብረ ሰዶማዊነትን “እስነዋሪ”፣ “ለባሕርይ የማይገባ”፣ እንዲሁም “ከተፈጥሮ ሕግና ሥርዓት ውጪ” እንደሆነ አጽንኦት ሰጥቶ ያስተምራል፡፡ በዚህ ሰዶማዊ ግብር ኃጢአት የሠሩት ወንዶች ብቻ ሳይሆኑ ሴቶችም እንደሆኑ ይናገራል፡፡
“ . . . ስለዚህ እርስ በርሳቸው ሥጋቸውን ሊያዋርድ እግዚአብሔር በልባቸው ፍትወት ወደ ርኲስነት አሳልፎ ሰጣቸው . . ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ፤ እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶች መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ ወንዶችም በወንዶች ነውር አድርገው በስሕተታቸው የሚገባውን ብድራት በራሳቸው ተቀበሉ፡፡” (ሮሜ. 1÷24-27)
“. . . ወይስ ዓመፀኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንዳይወርሱ አታውቁምን አትሳቱ ሴሰኞች ቢሆኑ ወይም ጣኦትን የሚያመልኲ ወይም አመንዝሮች ወይም ቀላጮች ወይም ከወንድ ጋር ዝሙት የሚያደርጒ . . . የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም፡፡” (ቆሮ. 6÷9-10)
ወጣቶች “ቀላጭ” ማለት ወንዳገረድ ለጾታው የማይገባ ዝሙትን ለመፈጸም እንደ ሴት ሆኖና ከወንድ ዘርን የሚቀበል ማለት ነው፡፡ እንደዚሁም ሴት ከወንዳ ወንድ ሴት ጋር ዝሙት ስትፈጽም ‹‹ቀላጭ›› ትባላለች፡፡
ማጠቃለያ፡-
ወንድሞችና እህቶች ግብረ ሰዶማዊነት በእግዚአብሔር የተጠላ ክፉ ግብር መሆኑን ተገንዝባችሁ ራሳችሁን ከዚህ ክፉ ተግባር ጠብቁ፡፡ ብዙ ንጹሐን ሰዎች በእነዚህ ክፉ ሰዎች እንዳይበላሹና ሰዶማውያን እንዳይሆኑ እውነታውን ማስተማር ግንዛቤ መፍጠር የሁላችሁም ሓላፊነት መሆኑን አንዘንጋ፡፡እንዲሁም በዚህ ህይወት ያሉትን ሰዎች በተቻለን መጠን መክረን ከዚህ ህይወት እንዲወጡ መፀለይ ያስፈልገናል እንዲሁም እዚህ ህይወት ውስጥ ያሉትን ሰዎች እግዚአብሔር መሀሪ እና ይቅር ባይ ፍቅር መሆኑን አምነው በንስሀ እንዲመለሱ ጥረት እናድርግ ፡፡እግዚአብሔር አምላካችን አገራችንን ቤተክርስቲያናችንን አለማችንን ከዚህ ክፉ መንፈስ ይጠብቅልን ከአለማችን ይህንን ክፉ መንፈስ ያጥፋልን አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፡-
1.ግብረ ሰዶማዊነት እና የሴቶች ክህነት/ብፁ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የቀድሞ ፓትርያሪክ እንደፃፉት ትርጉም ታደለ ፋንታ/ዲ/ን/
2. አባ ሳሙኤል ሰዶማውያንና የኃጢአት ደሞዝ (1998) ዓ.ም አዲስ አበባ፡፡እና ሁለተኛ እትም
3.የተለያዩ ድህረ ገፆች

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!!!

Saturday, May 16, 2015

በስቶክሆልም በሊቢያ ሕይወታቸውን ያጡ ኢትዮጵያውያን በደመቀ ሁኔታ ታስበው ዋሉ




ንኤል ሐረር ለዘ-ሐበሻ ከስዊድን እንደዘገበው:- 
ትላንት ሐሙስ ግንቦት 6/2007 በምስራቅ አፍሪካ እና አውሮፓ አህጉረ ስብከት የመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ እስቶኮልም ሆተርየት ባዘጋጀው የ21ኛው ክፍለ ዘመን ድንቅ የእግዚአብሔር ምስክሮች ለሆኑት 30 (ሰላሳ ) የኦርቶዶክስ ልጆች መታሰቢያ ፕሮግራም በዕለቱ ከተገኙ የግብፅ የሶርያ ብጹአን አባቶች ጋር በደማቅ ሁኔታ ታሥቦ ውሏል፡፡ 

በዕለቱ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን ካህንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ካህናት ተገኝተዋል። እንዲሁም በስቶኮልም ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ስንበት ት/ቤት ተማሪዎች የህብረት መዝሙረና በወቅቱ የነበረውን የሰማዕታቱን ጽናት የሚያሳይ ትዕይንት ፤የአበባ ማስቀመጥ እና የጧፍ ማብራት ፕሮግራሞ ተካሂዷል። 

Sunday, March 1, 2015

ሰበር ዜና: የወያኔ ሰላይ ከሆላንድ ተባረረ!

ሂሩት መለሰ – ከሮተርዳም
ሮተርዳም፣ ጥቅምት 28 ቀን 2015 – በስደት ስሙ አለማየሁ ስንታየው በመባል የሚታወቀው የህወሃት ሰላይ ከኔዘርላንድስ ተባረረ። አለማየሁ ስንታየሁ ቋሚ ነዋሪ ከነበረበት ከኔዘርላንድስ እንዲባረር የተደረገው በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በከፈቱበት የስለላ ክስ መሆኑም ታውቋል።
የሮተርዳም ከተማ ፍርድ ቤት በአለማየሁ ላይ የተመሰረተውን የስለላ ክስና ማስራጃ ለረጅም ጊዜ ሲመረምር ከቆየ በኋላ የግለሰቡ የመኖርያ ፈቃድ እና ቤት እንዲነጠቅ፣ የሆላንድን ምድርም በአስቸኳይ ለቆ እንዲወጣ ውሳኔ አስተላልፏል። ከሆላንድ የምመራ ቡድን እንደተረዳነው ከሆነ – የግለሰቡ ቤት ሲፈተሽ ወያኔ የሰጠው እውነተኛ መታወቂያ እና በርካታ የስለላ ሰነዶች ተገኝተውበታል። በእርዳታ ስም የተቋቋመለት ድርጅትም ተፈትሾ ማስረጃዎች እንደተገኙ ለማወቅ ተችሏል።

ይህ ሰው ትክክለኛ ስሙ ዘለቀ ፎላ ይባላል። በደርግ ጊዜ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባል ሆኖ ለረጅም አመታት አገልግሏል። ወያኔ ስልጣን ሲቆጣጠር ለፖለቲካ ተሃድሶ አዋሳ ደቡብ ጦር ቅጥር ግቢ ተላከ። በተሃድሶ በነበረበት ጊዜ ቁጥራቸው ብዙ የሆኑ የሰራዊቱ አባላትን ለወያኔ በማጋለጥ ታማኝነቱን ሲያሳይ እንደነበር የዚህ ዜና ዘጋቢ እማኝ ነው። የበርካታ ኢትዮጵያውያን ደም በእጁ ያለው አለማየሁ ከተሃድሶው ከወጣ በኋላ እስራኤል ገደቡ (የፓልቶክ ስሙ ኢዛና) ከተባለ ወታደር ጋር በመሆን የሰላም ተጓዥ ነኝ ብሎ በመገናኛ ብዙሃን ሲታይ ነበር። አለማየሁ እና ኢዛና በየሃገሩ እየዞሩ ስለ አዲሱ ስርዓት መልካምነት ሲሰብኩ ከረሙ። ከዚያም አስመራ ድረስ ተልከው የሻእቢያውን መሪ ኢሳያስ አፈወርቂን በወታደሩ ስም ይቅርታ ጠይቀዋል።

አለማየሁ እና ኢዛና ለወያኔ በሰሩት ውለታ ሆላንድ ገብተው እንዲቀሩ ተደረገ። ይህም የተደረገበት ምክንያት በአውሮፓ የሚኖሩ ኢዮጵያውያንን ተቃዋሚ በመምሰልና በረቀቀ መንገድ እንዲያበጣብጡና እንዲሰልሉ ነው።
በሆላንድ ሃገር የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቆ ለወያኔ ቡድን የስለላ ስራ መስራት ወንጀል ነው። አለማየሁ የሆላንድ ዜግነት ቢኖረው ኖሮ ቅጣቱ የከፋ ይሆን እንደነበር ጉዳዩን እየተከታተሉ ያሉ የህግ ባለሙያዎች ተናግረዋል።


የአለማየሁ መባረር በተሰማ ግዜ በሮተርዳም ያሉ የህወሃት ደጋፊዎች የአቤቱታ ደብዳቤ በመጻፍ ፊርማ ማሰባሰብ ቢጀምሩም ሊሳካላቸው አልቻለም። የአቤቱታ ደብዳቤው ግለሰቡ እዚህ የተወለዱ ሁለት ለጆቹን እየመጣ እንዲጎበኝ ይፈቀድለት የሚል ነበር።
አለማየሁ ስንታየሁ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከሆላንድ ተባረረ። ኢዛና ግን አሁን የተቃዋሚ ጭንብሉን አውልቆ በግልጽ ወያኔ መሆኑን መናገር ጀምሯል።


ኢዛና የሆላንድ ዜግነት ቢኖረውም በሆላንድ ሃገር ስራ ሰርቶ አያውቅም። የቀንና ማታ ስራው በፓልቶክ ላይ ነው። ባለፈው ወር ኢትዮጵያ የተጓዙ ዲያስፖራ ኢንቨስተሮችን እየመራ በቴሌቭዥን መግለጫ ሲሰጥ አይተነዋል። ይህ ትርኢት የወያኔ ኢንቨስተሮች በጨበጣ እንደሚንቀሳቀሱም ያሳየናል።

Thursday, February 26, 2015

ከአንድነት ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበርና ከሰማያዊ ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበር የተሰጠ የጋራ መግለጫ


  • 203
     
    Share
ANAASO Blueእንደሚታወቀው የኢህአዴግ አገዛዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ ጸረ ዲሞክራሲ አካሄዱ እየባሰበት የመጣና መሠረታዊ መብቶችን ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ ማፈኑን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡ በቅርቡ በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲ ላይ አገዛዙ በሚያዝዛቸው የተቋማት ኃላፊዎች ቀጭን ትዕዛዝ የፓርቲዎቹ ሕልውና ለጥቂት ግለሰቦች ተላልፎ ተሰጥቷል፡፡ ይህ ዓይነቱ ህገ-ወጥ ድርጊት መቼዉም ቢሆን ተቀባይነት አይኖረውም! ለአገራችን የሠላማዊ የስልጣን ሽግግር ከባድ መሠናክል ሊሆን እንደሚችል ሁሉም ይገነዘባል ብለን እናምናለን፡፡ የኢህአዴግ የምርጫ ቦርድ እንዲህ ዓይነቱን ክፉ ስራ ሲወስን የአገራችንን የረጅም ሠላም አይተው ሣይሆን በአገዛዙ ቁንጮ ሰዎች በመታዘዝ በተቋም ስም የሚሠሩት የማደናገር የድንቁርና ተግባራቸዉ አንድ አካል ነው ብለን እናምናለን፡፡ ማህበራችን ይህን ድርጊት እጅጉን ያወግዛል። በመሆኑም ድርጊቱን በጋራ እንቃወማለን።
በምርጫ ቦርድ ስም የተወሰነው ህገ-ወጥ ውሣኔ ምክንያት መላ የአንድነትና የመኢአድ አባላት የፖለቲካ እንቅስቃሴአቸው ተገድቧል፡፡ ይሁን እንጂ ለአገራቸው ካላቸው ፅኑ ፍቅር አኳያ ትግሉን ለማስቀጠል ከሠማያዊ ፓርቲ ጋር አብሮ ለመሥራት የአባልነት ፎርም በመሙላት ትግሉን ቀጥለዋል፡፡ ይህ ዓይነቱ የአባላት ቆራጥ ውሣኔ ሊበረታታና ሞራል ሊሰጠው የሚገባ ነው ብለን እናምናለን! እኛም በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ የሁለቱ የድጋፍ ማህበራት ሙሉ በሙሉ ድጋፋችንን እንደምንሰጥ እናረጋግጣለን፡፡
ስለሆነም በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ የአንድነትና የሠማያዊ የድጋፍ ማህበራት በጋራ በኮሜቴ ደረጃ ተዋቅረን በዋና ዋና ጉዳዬች ላይ ማለትም በፋይናንስ፤ በእስረኞች ጉዳይ እና በዲኘሎማሲው ዙሪያ ሙሉ በሙሉ በትብብር አብረን እየሠራን የሰማያዊ ፓርቲንና ሌሎች በሃገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ሃይሎችን በጋራ ድጋፍ ለመስጠት ውሣኔ አሣልፈናል፡፡ በቀጣይም በጋራ የኮሚቴ ውይይቶችን እያደረግን ለሰማያዊ ፓርቲ የሚያስፈልጉ የሞራልና የማቴሪያል ርዳታ እንደምንሰጥ እናረጋግጣለን፡፡
የሰማያዊና የአንድነት ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበራት
የካቲት 19 2007 ዓ/ም
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39330#sthash.Jbph1yVo.dpuf

ESAT

http://ethsat.com/video/esat-daily-news-amsterdam-february-26-2015-ethiopia/#

Wednesday, December 10, 2014

ፖሊስ እስረኞቹን ነጥሎ ለማጥቃት እየጣረ ነው


‹‹አብረውን የታሰሩት ካልተፈቱ ብቻችን አንወጣም፡፡›› ሴት እስረኞች
ፖሊስ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት ታፍሰው የታሰሩትን አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎችን ነጣጥሎ ለማጥቃት ጥረት እያደረገ መሆኑን የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ በሰልፉ ወቅት ከታሰሩት መካከል በዛሬው ዕለት አብዛኛዎቹ ሴት ታሳሪዎችና የተወሰኑ ወንዶች ብቻ የመታወቂያ ዋስ አምጥተው እንዲወጡ የተነገራቸው ቢሆንም ታሳሪዎቹ ‹‹አብረውን የታሰሩት ካልተፈቱ በስተቀር ብቻችን አንወጣም፡፡›› እንዳሉ ተሰምቷል፡፡

በጉዳዩ ያነጋገርናቸው አቶ ዮናታን ተስፋዬ ‹‹ፖሊስ በተመሳሳይ ወንጀል ያዝኳቸው ያላቸውን ሰላማዊ ታጋዮች አንዱን በመታወቂያ ዋስ ውጣ ብሎ ሌላውን አስሮ በማቆየት ልዩነት የፈጠረው በዚህ አጋጣሚ ያሰጉኛል የሚላቸውን አመራሮችና ግለሰቦች ለማጥቃት ቀዳዳ እየፈለገ እንደሆነ ያሳያል›› ሲሉ ገልጾልናል፡፡
ለአዳሩ ሰልፍ ቅስቀሳ ላይ እያሉ በተመሳሳይ ጉዳይ ታስረው ከነበሩትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መካከል አንዳንዶቹን በመፍታት ስጋት ይፈጥሩብኛል ብሎ የሚያስባቸውን በተለይም የፓርቲውን አመራሮች አሁንም ድረስ አስሮ እንደሚገኝ በመግለጽ ስልቱ የተለመደ ነው ያሉት አቶ ዮናታን አሁን በአንድ በኩል እየደረሰበት ያለውን ጫና ለማርገብ የተወሰኑትን በመፍታት አመራሮቹን ለማጥቃት የተደረገ ስልት ነው ብለዋል፡፡
ገዥው ፓርቲ በሰልፉ ላይ በተገኙት አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ላይ በፈጸመው ጭካኔ ከደረሰበት ጫና በተጨማሪ ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ በሚፈጸምባቸው በደል አዲስ አበባ ፖሊስ (ሶስተኛ) የሚገኙት እስረኞች ዛሬ ታህሳስ 1/2007 ዓ.ም የርሃብ አድማ መጀመራቸውና ፖፖላሬ የሚገኙትም እስር ቤት ሆነው ትግላቸውን እንደሚያጠናክሩ መግለጻቸው ስርዓቱን ጫና ውስጥ እንደከተተው የገለጹት የህዝብ ግንኙነቱ ፖሊስ በህገ ወጥ መንገድ የያዛቸውንና ጭካኔ የፈጸመባቸውን ሁሉንም እስረኞች ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታና መነጣጠል ሊፈታ ይገባል ብለዋል፡፡
ከነገረ  ኢትዮጲያ

በፍቃዱ አበበ ወደ ቂሊንጦ ተዛወረ፡፡



በ‹‹ሽብርተኝነት›› ተከሶ ለሶስት ወር ያህል ማዕከላዊ እስር ቤት የቆየው የሰማያዊ ፓርቲ የአርባ ምንጭ ሰብሰቢ አቶ በፍቃዱ አበበ ወደ ቂሊንጦ መዛወሩ ተነገረ፡፡ በዛሬው ዕለት የፓርቲው አባላት ወደ ማዕከላዊ በማቅናት በጠየቁበት ወቅት ፖሊስ በፍቃዱ አበበ ወደ ቂሊንጦ እንደተዛወረ ገልጸውላቸዋል፡፡
በሌላ በኩል ከሰላማዊ ሰልፉ በፊት ታፍና የታሰረችው ወይንሸት ንጉሴ የምትገኝበት ቤላ 18 ተብሎ የሚጠራ እስር ቤት ‹‹ሰማያዊ ናችሁ›› ተብለው ተጨማሪ ሴቶች መታሰራቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

Tuesday, December 9, 2014

ዴሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጲያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ አቋም መግለጫ ፡፡

 DCESON    DCESON


ዴሞክራሲያዊ ውጥ በኢትዮጲያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ  ከተቋቋመበት አላማዎች አንዱና ዋነኛው በሃገራችን  በኢትዮጲያ ያለውን ኢፍትሃዊ የአንድ ዘር የበላይነት የሰፈነበትን አምባገነን  ስርሃት በማውገዝ እንዲሁም በመታገል ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጲያን ማለትም  የዜጎችን እኩልነት የተረጋገጠባት፣  የህዝብ የስልጣን ባለቤትነት የተረጋገጠባት ፣ የዜጎች ሰብአዊ መብት የተከበረባት ፣  የህግ የበላይነት የሰፈነባት፣ እንዲሁም  ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በኩል አይን የሚታይባት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጲያን ለመገንባት የሚደረገውን ህዝባዊ ትግል መደገፍና ብሎም በአጋርነት ሞቆም ነው፡፡

ስለሆነም ባሳለፍነው ሳምንት ማለትም ህዳር 27/28 የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የሃገሪቱ ህገ- መንግስት በሚፈቅደው መሰረት  ለሃያ አራት ሰአት የሚቆይ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርተው እንደነበረ ይታወሳል፡፡ ሆኖም በማን አለብኝ ሃገሪቱን እንዳሻው የሚያደርግ ህውሃት(ኢህአዴግ)አሁን በህብረተሰቡ ዘንድ የተፈጠረውን የለውጥ ስሜት እንዲሁም ለዚህ ክስተት ምክኒያት ናቸው ያላቸውን የ9ኑ ፖርቲዎች ትብብር ከመቼውም በላይ ስላሰጋው ከላይ  በተጠቀሰው ቀን የአደባባይ የ24 ሰአት ሰልፍ እንዳይካሄድ የትብብሩን አምራሮችና አባላትን በማዋከብ ስራ በዝቶበት ሰንብቷል፡፡

በመጨረሻም በሰልፉ ላይ የተገኙ የ9ኙ ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮችና አባሎችን እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ፍርሃት ባሸበረው ህውሃት (ኢህአዴግ)በጭካኔ ተደብድበዋል፣ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፣ ተግዘው ታስረዋል፡፡ ሙስሊሙ ማህበረሰብ  በሰላማዊ ሰልፉ ላይ በመገኝታቸው ብቻ ከጎዳና ታፍሰው የአገዛዙ አረመኔዊ እርምጃ ሰለባ ሆነዋል፡፡ እስካሁንም በዚሁ ዘረኛና አረመኔያዊ አገዛዝ ቁጥራቸው ከ300 የሚበልጡ  ሰላማዊ ታጋዮች በእስር ቤት ታፍነውከፍተኛ ድብደባ ደርሶባቸዋል ፡፡
ዴሞክራሲያዊ ውጥ በኢትዮጲያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ  አምባገነኑ ህውሃት(ኢህአዴግ) በሰላማዊ ታጋዮች እንዲሁም በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ሊያሰሙ በወጡ ዜጎች ላይ የወሰደውን አረመኔያዊ እርምጃ በጥብቅ እያወገዘ የ9ኙ ፖርቲዎች ትብብር እያደረገ ያለውን እልህ አስጨራሽ ትግል በንቃት የሚከታተልና ከጎናችሁ መቆሙን እየገለጸ ለተጀመረው የነጻነት ትግል አጋርነቱን ይገልጻል፡፡
ድል ለኢትዮጲያ ህዝብ!!!!!
ዴሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጲያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ !!

በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የተካሄደውን ድብደባና እስራት እናወግዛለን


ህዳር 27፣ 2007

 ቅዳሜ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ. ም (ዲሴምበር 6፣ 2014) በዘጠኝ ተቃዋሚ ድርጅቶች አስተባባሪነት በአዲስ አበባ ተጠርቶ በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የህወሀት/ ኢህአዴግ አገዛዝ የጸጥታ ሰራዊት ህዝቡን በዱላ በመደብደብና ብዙዎችን ወደ  እስር በመወርወር ሰላማዊ ሰልፉን በትኗል። 
የዚህ ግፍ ሰለባ ከሆኑት ውስጥም የትብብሩ ሰባሳቢ ኢንጅነር ይልቃል  እነደሚገኙበት ታውቋል። ይህን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ሽንጎው አጥብቆ ያወግዛል። በግፍ የታሰሩት ሁሉ ባስቸኳይ እንዲፈቱም ይጠይቃል።  –-[ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

Monday, November 24, 2014

ለስብሰባ ሲቀሰቅሱ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ተጨማሪ 7 ቀናት ተቀጠረባቸው፡፡




  • 16
     
    Share
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡ባለፈው የፍርድ ውሎ ታሳሪዎቹ ህጋዊ እውቅና ለተሰጠው ስብሰባ የቀሰቀሱ መሆኑን ጠቅሰው መታሰራቸው ህገ ወጥ በመሆኑ እንዲፈለቀቁ ቢከራከሩም፤ ፖሊስ ‹‹ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ስላልተያዙ መያዝ አለብን፡፡
 እነሱም ከተለቀቁ መረጃ ያጠፉብናል›› በሚል የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተቀባይት አግኝቷል ለዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አንድ ሳምንት ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዶለታል፡፡ በአንጻሩ ታሳዎቹ የቀረቧቸው ቅሬታዎችና መከራከሪያዎች ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡

Sunday, November 23, 2014

ለፊልም ቀረጻ ሜካፕ በገባለት የዓይን ኮንታክት ሌንስ የተነሳ የዓይን ብርሃኑን ለአንድ ቀን አጥቶ ዋለ ።

ታዋቂው አርቲስት ባልተጠና የፊልም ቀረጻ ሜካፕ በገባለት የዓይን ኮንታክት ሌንስ የተነሳ የዓይን ብርሃኑን ለአንድ ቀን አጥቶ ዋለ

ከዘላለም ገብሬ

shimelis abera joro

ለፊልም ስራ ወጥቶ በለበሰው ቀረጻው የኮንታክት ሌንስ ምክንያት አይኖቹ ለአንድ ቀናት ላለማየት ችሎ ነበር ። ይህም ሊሆን የቻለው የአይን ብሌኖቹ ውስጥ ተሰክተው የነበሩት ኮንታክት ሌንስ ለፊልሙ ስራ ሲባል እንዲያጠል የታዘዘ ሲሆን የአይኖቹን ብሌኖች ላይ ጫጭረውትተንደነበርረና ለረጅም ሰአታት አይኖቹ ሲያለቅሱ እንደነበር እና ጉዳቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እየጨመረ የመጣው የአይኑ ማልቀስ ሥሜት እስከ ሆስፒታል ድረስ እንዲሄድደና በባለሙያዎች እንዲታይ ተደርጎ መድሃኒት እንዲጠቀም አዘውት ነበር “ነገ እኮ ቴአትር አለኝ” እያለ ለቲያትር ስራው የሚጨነው አበራ ጆሮ በዶክተሮቹ ጫና አንተ አይንህ እየጠፋ ስለ ነገ ቴአትር ታስባለህ ሲሉት ምላሽ ሰጥተውታል ።
ይህ በእንደዚህ እንዳለ ችግሩ እንዲቀል በታዘዘው መዳኒት ታግዞ እስከሚቀጥለው ማለዳ እንዲቆይ ታዟል:: በዚህ የከፋ ሁኔታ የሚደርስበት ከሆነ ግን ወደ ከፍተኛ ህክምና ለኦፕራሲዮን ሊላክከንደሚችልላሳውቀውት ተለይተዋል ።

ሆኖም ግን ከአንድ ቀን በሁዋላ አይኑ ዳግም ወደ እይታ ሊመለስ እንደቻለ ኢትዮጲካን ሊንክ ጠቁⶁል ። ሆኖም ግን ከጥንቃቄ ጉድለትና የባለሙያዎች ድጋፍ ባለመኖሩ ለተደረገለት የሜካፕ ስራ አርቲስት ሽመልስ አበራ የቴአትርራ አጋጆቹን ለመክሰስ አለመክሰስ የተደረገ ምን አይነት መረጃ እንዳልተገለጸ ሲሆን ፣በሃገራችን በሚደረጉት የፊልምና የቴአትር ስራዎች ላይ የሜክአፕ አርቲስት ሆነው የሚያገለግሉት በሙሉ በሙያቸው ዘርፍ ሳይሆን ያለሙያቸው በመሆኑ ለብዙ ጉዳቶች ይዳጋል ።ይህንን ደግሞ ከግንዛቤ በማድረግ ለአይንም ሆነ ለሌላ የአካል ስራ መዋል ያለበት በሙያው ላይ የተካነ መሆን ይገባዋል።
ለእያንዳንዱ የአካል ስራ እንቅስቃሴ ሙያዊ እገዛን የሚጠይቅ ሲሆን ለአንድ ፊልም ደራሲ አዘጋጅ ፣ዳይሬክተር ወይንም ሌላም ሌላም አንድን ሰው ብቻ ማእረግ በመስጠት በሚሰራበት የኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ ይህ ኁኔታ መቀጣጫ ሊሆናቸው የሚገባ ሲሆን ፣ሽመልስ አበራ ጉዳዩን ከምን ሊያደርሰው እንደሚችል አልታወቀም ።

በብርቱ ታምሜአለው አበበ ቀስቶ ከዝዋይ እስር ቤት


30 ለደቂቃዎች  በዝዋይ እስር ቤት (ግዞት) 
(ነገረ ኢትዮጽያ)

November 23/2014
በላይ ማና

ለመድረስ 2 ሰዓት በላይ ጉዞ ማድረግ ነበረብን፤ በጠዋት ቃሊቲ መነሐሪያ በመገኘት የዝዋይን ትራንስፖርት ለመያዝ ስንገኝ መልካም አጋጣሚ ተከሰተ፡፡ አጋጣሚው እኛ ወደምንሄድበት ዝዋይ እስር ቤት ሊሄዱ የተሰናዱትን የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም እና ሌላ የስራ ባልደረባውን ያገናኘ ነበር፡፡ ቁጥራችን መጨመሩ ለእኛም ለምንጠይቃቸው እስረኞችም መልካም ነበር፡፡

ከተማዋ እንደደረስን ወደ አንድ አብረውኝ የተጓዙት ወዳጆቼ የሚያውቁት ቤት አመራን፤ ቡና በፔርሙስ ለመያዝ፡፡ ‹‹ተመስገን ደሳለኝ በእጅጉ ቡና ይወዳል አለኝ›› ታናሽ ወንድሙ፡፡ ቡናውን አስቀድተን ከከተማዋ ትንሽ ወጣ ብሎ ወደሚገኘው እስር ቤት አመራን፡፡ ጉዞው ደግሞ በጋሪ ነበር፡፡ ወደእስር ቤት የሚወስደው መንገድ እጅግ አቧራማ በመሆኑ ተጓዦች አቧራውን መልበሳቸው እሙን ነው፡፡ በእግር ለመጓዝ የፈቀደ ካለ ድልህ ቲባን በጫማዎቹ ልክ ይዋኝበታል፡፡ የእኛ ጉዞ በጋሪ ቢሆንም ከአቧራው ማምለጥ ግን አይቻልም፡፡

እስርቤቱ በር ደርሰን ከጋሪ እንደወረድን ወደጥበቃዎቹ ቀርበን የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስም ሰጥተን የእኛን ሙሉ አድራሻ አስመዘገብን፡፡ የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስናስመዘግብ ‹‹ምኑ ነህ?›› የሚለው ጥያቄ ይነሳል፡፡ ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድእያልን አስሞላን፡፡ መዝጋቢ ፖሊሶቹ ቀና እያሉ በጥያቄ ያዩናል፡፡ ኢትዮጵያውያን ወገኖችጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…› ተብለው እንጂ ሌላ በምን ይገለጻሉ ታዲያ! በዚህ መሰረት የአራት እስረኞችን ስም አስመዘገብን፤ እነሱም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ / አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ ናቸው፡፡ ጥብቅ ፍተሻውን አልፈን ልናያቸው የጓጓንላቸውን እስረኞች ወደምንገናኝበት ቦታ አመራን፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ቦታው ላይ ስንደርስ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በሶስት ፖሊሶች ተከብቦ ቀድመውን ከደረሱ ወዳጆቹ ጋር እያወራ ነበር፡፡ ከአጥር ወዲህ እና ወዲያ ማዶ ሆነን ግማሽ አካል ተቃቅፈን ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ ደስ አለን፤ ተመስገንም ደስታው በመላ ፊቱ ሲበራ ተመለከትን፡፡ በደስታው ድጋሜ ደስ ተሰኘን፡፡ በእኛ በኩል ትንሽ ስለ ጤንነቱ፣ በእሱ በኩል ስለቤተሰብ እና ስለእኛ ደህንነት ተጠያየቅን፡፡ በመካከላችን ትንሽ ዝምታ ሰፈነ፡፡ እኛም ተመስገንም ቀና ብለን ፖሊሶችን ተመለከትን፡፡ ከዚያም ተመስገን ጥያቄ ወረወረ፡፡ውጭ ያለው እንዴት ነው? አንድነትና ሰማያዊ….›› ተሜ የጀመረውን ሳይጨርስ ሁለቱ ፖሊሶች አንባረቁብን፡፡

‹‹
ፖለቲካ አታውራ! እናንተ ፖለቲካ አታውሩ! ዝም ብላችሁ ሌላ ሌላ አውሩ!…›› አሉን ፖሊሶች አንዴ እኛን አንዴ ከአጥር ማዶ የተቀመጠውን ተመስጋንን እየተመለከቱ፡፡የፖለቲካ ድርጅቶችን ስም መጥራት ፖለቲካ ማውራት ሆኖ ተሰማቸው፣ እዚያ ለነበሩ ፖሊሶች፡፡ የአንድነትን እና የሰማያዊን ስም ጠርቶ ተሜ ምን ሊያወራ እንደፈለገ እንኳ ለመስማት አልተዘጋጁም፡፡ በየዕለቱ መረጃ የሚያነፈንፍ፣ ያገኘውን መረጃ ደግሞ ወደህዝብ የሚያደርስ ሙያ ላይ እንደነበር ለእነሱ አልገባቸውም፡፡ አዎ መረጃ ምን ያህል እንደሚርብ ለፖሊሶቹ የተገለጸላቸው አልመሰለኝም፤ ለዚያውምለጋዜጠኛ፡፡

ተሜ ጋር ልናወራ ያሰብነው ብዙ አብይ ጉዳዮች ቢኖሩም ክልከላው የሚያወላዳ አልሆነም፡፡ በበኩሌ በኋላ ተመስገን ላይ ሊያደርሱበት የሚችሉት ጫና ይኖራል ከሚል ርዕሱን መቀየሩን መርጬ ነበር፡፡ ተመስገን ግን ‹‹እናውራበት›› በሚል ትንሽ ከፖሊሶቹ ጋር ተከራከረ፡፡ ተሜ ድፍረቱ በብዕሩ ብቻ አይደለም፡፡ መብቱን ለማስከበር ወደኋላ የማይል ብርቱ ሰው መሆኑን ከሁኔታው አነበብኩ፡፡በመሐል ላይ ሌሎች እስረኞችን እንዲጠሩልን ስም ዝርዝር ሰጥተን ስለነበር ሲዘገዩ ጊዜ ‹‹እነ ክንፈሚካኤልና አሳምነውን ጥሩልን እንጂ!›› አልናቸው፡፡

አንደኛው ፖሊስ ቆጣ ብሎ ‹‹ቆይ እሱ ጋር ጨርሱ!›› አለን፡፡ ከተመስገን ጋር ያለንን ቆይታ ማለቱ
ነበር፡፡ እኛም እስኪመጡ እንደምንጨርስ በመጥቀስ አስጠሩልን አልናቸው፡፡ በዚህ መሐል ትንሽ ጭቅጭቅ ድጋሜ ተፈጠረ፡፡ ‹‹እንዲያውም ስማቸውን በትክክል አልጻፋችሁም፤ ስለዚህ አንጠራላችሁም አሉን፡፡›› እኛም የሰጠናቸውን የስም ዝርዝር የጻፉት የራሳቸው ባልደረቦች እንጂ እኛ አለመሆናችንን ጠቅሰን ነገርናቸው፡፡ካፈርኩ አይመልሰኝ በሚመስል መልኩ አንጠራላችሁም አሉን፡፡ ‹‹በቃ አምጣው እንደገና አስተካክለው እንዲጽፉ አድርገን  እናምጣው!›› አልናቸው፡፡በእርግጥ ትክክለኛ ምክንያታቸው የስም ስህተት እንዳልሆነ እናውቅነበር፡፡

ሲጀመር አሳምነው ፅጌን ከእኛ ከወጣቶች ይልቅ እነሱ ከበረሃ ጀምረው ጠንቅቀው ያውቁታል፡፡ ስለሆነም ‹‹እገሌ የሚባል ሰው የለም፤ እዚሁ ተወለደ ካላላችሁን›› እያሉ ሲናገሩ በውስጤ እየሳቅሁ ነበር፡፡
እንዲያውም፣ ‹‹አዲስ ታሰረ ካላላችሁ በቀር አዲስ እንደማይወለድ ታውቃላችሁ፤ ሴትና ወንድ የት ይገናኛሉና ነው!›› አልኩ፡፡ የግዳቸውን ፈገግ አሉ፡፡በዚህ መሰል ጭቅጭቅ ከተመስገን ጋር ያለንን ጊዜ ተሻሙብን፡፡ ይህ የገባው ተመስገን ደሳለኝ በጭቅጭቁ ጣልቃ ገብቶ፣ ‹‹ሰዎቹ ከአዲስ አበባ ነው የመጡት፡፡ ስለሆነም ከሩቅ ቦታ መጥተው ሳያገኟቸው ቢመለሱ ደስ አይልም›› አላቸው፡፡ ወዲያው አንደኛው ወደ እኛ ዞሮ ‹‹ናትናኤል መኮንንን የት ነው የምታውቀው?›› አለኝ፡፡ ጥያቄውን ወደጓደኛየም ወሰደው፡፡

‹‹ይህን ጥያቄ ምን አመጣው›› ብዬ ጥያቄውን በጥያቄ ከመመለሴ፣ ጋዜጠኛ ተመስገን ቀበል አድርጎ
‹‹
ኢትዮጵያዊ ወገኑን ሳያውቀውም ቢሆን መጠየቅ ይችላል!›› አለ፡፡ ተመስገን ተቆርቋሪነቱ ደስ ይላል፡፡ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ እስረኞቹ ሊጠሩልን ስምምነት ላይ ደረስን፡፡ እስኪመጡ ድረስም ከተመስገን ደሳለኝ ጋር ‹‹ከፖለቲካ ውጭ›› ባለ ድባብ ጨዋታችንን ቀጠልን፡፡ተሜ ስለሚዲያ አብዝቶ ጠየቀኝ፡፡ ያለው ሁኔታ ከሚያውቀው እውነታእንዳልተለወጠ ገለጽኩለት፡፡ ከዚያም ወደወንድሙ ዞሮ ስለቤተሰባዊ ጉዳዮች ሲያወራ ዓይኖቼን ወዳስጠራናቸው እስረኞችመምጫ አማትር ያዝኩ፡፡

/ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ ከርቀት አንድ ላይ ሆነው ሲመጡ ተመለከትኩ፡፡ ከፖሊሶች ጋር ባለው እሰጣ ገባ ስሜቴ ተረብሾ ነበር፡፡ ይህ ስሜቴ ግን ድንገት
ሶስቱ ሰዎች ከርቀት በፈገግታ ታጅበው ወደ እኛ ሲመጡ ሳይ በንኖ ጠፋ፡፡ሞገደኛው አበበ ቀስቶ እና የተጓደለው ጤናው ጉዳይ / አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ) ካለንበት ስፍራ ደርሰው ተቃቅፈን ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ አቤት እንዴት ደስእንዳላቸው! ሙሉ ፊታቸው ያበራል፡፡ ‹‹እኛን ልትጠይቁ መጣችሁ?›› እያሉ በደስታ ተቁነጠነጡ፡፡

እውነት ለመናገር ደስታው የእነሱ ሳይሆን የእኛ ነበር፡፡ በበኩሌ በእስር ላይ ያሉ ወንድም እህቶቼን መጠየቅ ምን አይነት የህሊና እረፍትና ደስታ እንደሚሰጠኝ የማውቀው እኔው ነኝ፡፡ይህደስታችን ታዲያ ተመስገን ደሳለኝ ጋር በነበረው መልኩ ድንገት ደፈረሰ፡፡ ፖሊሶቹ አሁንም እሳት ለበሱ፡፡ከውጭ ያለውን ነገር የተራቡት እነ ክንፈሚካኤል እነዚያን የፓርቲ ስሞች ጠቅሰው ጥያቄ ሰነዘሩ፡፡ ‹‹አንድነትና ሰማያዊ…›› ካፋቸው ቀልበው ፖሊሶቹ አንባረቁ፡፡ ‹‹አንተ ፖለቲካ አታውራ!›› በማለት ያዙኝ ልቀቁኝ አሉ፡፡ እንዲያውም ምንም ሳናወራ ተነሱና ግቡ አሏቸው፡፡ በዚህ ጊዜ አበበ ቀስቶ በኃይለ ቃል መልሶ ፖሊሶቹ ላይ አፈጠጠ፡፡ፖሊሶቹ ትንሽ ድንግጥ በማለት ‹‹ሌላ ሌላ አውሩ በቃ!›› አሉን፡፡

ዝዋይ እስር ቤት ካሉ እስረኞች ጋር የሚገናኝ ጠያቂ ‹‹ደህና ነህ፣ እንዴት ነህ…›› ብቻ ብሎ እንዲመለስ ነው የሚፈለገው፡፡ከሁሉም ጋር ያለውን ማህበራዊና የጤና ሁኔታ አንስተን ስንጨዋወት አበበ ቀስቶ ወደእኔ አንገቱን ሰገግ አድርጎ ‹‹አሞኛል፣ በብርቱ ከታመምኩ ቆይቻለሁ›› አለኝ፡፡ ከዚህ ቀደም በጤናው ላይ እከል እንደገጠመው አውቅ ነበር፡፡ የአሁኑ ህመሙ ምን ይሆን በሚል የበለጠ እንዲነግረኝ እኔም አንገቴን ሰገግ አድርጌ ጆሮዎቼን ሰጠሁት፡፡‹‹የሚያመኝ ይሄን የጆሮየን አካባቢ ነው፡፡ በብርቱ ታምሜያለሁ፡፡ አብሮኝ የሚተኛው ናትናኤል መኮንን ባይሆን ኑሮ ምን እንደሚውጠኝ አላውቅም፡፡

 ቁስል አበጅቶ መጥፎ ጠረንም ፈጥሯል›› አለኝ፡፡ እኔም የህመሙ ምክንያት ምን እንደሆነ ጠየቅኩት፡፡‹‹ያኔ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ እያለሁ የደረሰብኝ ድብደባ ነው ዛሬም የሚያሰቃየኝ›› አለኝና ከዚያ ወዲህ እንዴት እየተሰቃየ እንዳለ አስከትሎ አስረዳኝ፡፡ እኔም ‹‹ህክምና…›› ሳልጨርሰው ተቀበለኝ፡፡ ‹‹ህክምና የሚባለውን ተወው፡፡ ይሄው ስንት ጊዜ እንዲያሳክሙኝ የምጮኸው! ሰበቡአያልቅባቸውም! ምንም በቂ ህክምና አላገኘሁም፡፡ መቼስ….›› ብሎ ከደቂቃዎች በፊት በሳቅ፣ ከዚያም በንዴት ውስጥ የነበረው ቆፍጣናውና ቀጭኑ ፖለቲከኛ በትካዜ አንገቱን ደፋ፡፡ውስጤ በማላውቀው ስሜት ተላወሰ፡፡ አበበ ቀስቶ በስካርቭ ጨርቅ ሙሉ ጆሮ ግንዱን ጠምጥሞ የመጣበት ምክንያት ገባኝ፡፡ ቁስሉን ለመሸፈን ነው፡፡

ከአበበ ጋር ይህን ስናወራ ሌሎች ወዳጆቼ ከእነ አሳምነው እና ናትናኤል ጋር ስለተለያዩ ጉዳዮች (‹ከፖለቲካ ውጭ›) እያወሩ ነበር፡፡ ‹‹እስኪ ደግሞ ከእነሱ ጋር አውራ፣ ጊዜህን እኔ ብቻ ወሰድኩብህ›› አለኝ አበበ ቀስቶ ወደ ናትናኤልና አሳምነው እየተመለከተ፡፡ እኔም በአለችው ትንሽ ደቂቃ ከሌሎቹ ጋር ጨዋታ ያዝኩ፡፡ በዚህ መሐል ግን ቀልቤ የአበበ ቀስቶ ጤንነት ላይ ነበር፡፡እንዴት ሰው አካሉ እንዲያ ቆስሎ ህክምና አይሰጠውም? ስንብት በፖሊሶች ተደጋጋሚማሳሰቢያ ለሰላሳ ደቂቃዎች ብቻ የነበረን ቆይታ ማብቃቱን ስንረዳ 30 ደቂቃ ምን ያህል አጭር እንደሆነ ተገነዘብን፡፡

ስድስት ሰዓት ደርሶም ስለነበር መለያየታችን ግድ ሆነ፡፡ ስንገናኝ እንዳደረግነው ሁሉ እንደገና ለስንብትም ተቃቀፍን፡፡ በእቅፎቻችን መካከል የተሰነቀረው አጥር ደግሞ የመለያየታችን ደንቃራነት ማሳያ ነበር፡፡

ከእነ አበበ ቀስቶ ጋር ያለኝን ስንብት ጨርሼ ወደ ተመስገን ደሳለኝ ስጠጋ በእጆቹ አንገቴን ሳብ አድርጎ ወደ ጆሮዬ ጠጋ ማለት ‹‹ስርዓት ሲፈርስ የሚያደርገውን ያጣል፡፡ ስርዓቱ እየፈረሰ ነው›› አለኝ፡፡ ምንም አልመለስኩለትም፡፡