Saturday, November 16, 2013

“የኛ ዜጐች በሳውዲ ከሰውነት በታች ተዋርደው ግፍ የሚደርስባቸው ለዜጐች የሚቆረቆር መንግስት ስለሌለ ነው”

“ለዜጐቻችን ስቃይ የሳኡዲና የአገራችን መንግስታት ተጠያቂ ናቸው” ተቃዋሚ ፓርቲዎች

NOV 16,2013

ሠሞኑን በሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ እየደረሠ ያለው ግፍና ስቃይ እንዳሳዘናቸው የገለፁ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፤ የሣውዲ አረቢያ መንግስት እና የኢትዮጵያ መንግስት የመጀመሪያ ደረጃ ተጠያቂ ናቸው ሲሉ ተናገሩ፡፡ የመድረክ ሊቀመንበር ዶ/ር መራራ ጉዲና፣ ሣውዲ አረቢያ የራሷንም ዜጐች መብት የማታከብር ሃገር መሆኗን ገልፀው፣ በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመው አሠቃቂ ስራ ግን በ21ኛው ክ/ዘመን የማይጠበቅ ግፍ ነው ብለዋል። በተለይ በሴቶች ላይ የሚፈፀመው ድርጊት አስነዋሪ ነው በማለት መወገዝ እንዳለበት የተናገሩት ዶ/ር መራራ፤ ዋናው ተጠያቂ የሳውዲ መንግስት ነው ብለዋል፡፡
“በሌላ በኩል ኢህአዴግ ሃገሪቱን የስደት ሃገር አድርጓል” ያሉት ዶ/ር መረራ፤ በሜድትራኒያን፣ በየመንና በደቡብ አፍሪካ መስመሮች የሚሰደዱ ዜጐቻችን የአውሬ ሲሣይ እየሆኑ ነው፤ በሃገር ውስጥም በውጭም የዜጐቹን መብት ማስከበር ያልቻለው የኢትዮጵያ መንግስት ተጠያቂ መሆን አለበት” ብለዋል፡፡
በሣውዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ በትኩረት እየተከታተሉ መሆናቸውን የሚገልፁት የመኢአድ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ መንግስት በዜጐቻችን ላይ የተፈፀመውን ድርጊት ለመከላከልና ለማስቆም አለመቻሉ መንግስት አልባ መሆናችንን የሚያሣይ ነው ብለዋል፡፡ አቶ አበባው እንደሚሉት፤ የሌላ ሃገር መንግስት ቢሆን ኖሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን እዚያ ሃገር ድረስ ልኮ ሄዶ የዜጐቹን መብት ያስከብር ነበር ብለዋል – አቶ አበባው፡፡ እዚህ ሃገር የውጭ ዜጐች ከቀን ሠራተኛነት ጀምሮ በተለያዩ የስራ መስኮች ላይ መብታቸው ተከብሮላቸው ይኖራሉ ያሉት አቶ አበባው፤ “የኛ ዜጐች በሳውዲ ከሰውነት በታች ተዋርደው ግፍ የሚደርስባቸው ለዜጐች የሚቆረቆር መንግስት ስለሌለ ነው” ብለዋል፡፡ ለዜጐቻችን ሠቆቃ የመጀመሪያ ደረጃ ተጠያቂው የኢትዮጵያ መንግስት ነው በማለት የሚናገሩት አቶ አበባው፤ ዜጐች በሃገራቸው የስራ እድል የሚያገኙበትን አማራጭ ማስፋት የመንግስት ሃላፊነት ቢሆንም፤ በተቃራኒው በአዲስ አበባም ሆነ በሌሎች ከተሞች ብሎኬት የሚሠሩት፣ ሹፌር የሚሆኑት፣ አሣማ የሚያረቡትና የመሣሠሉትን ስራዎች የሚሠሩት የውጭ ሃገር ዜጐች ሆነዋል” ብለዋል አቶ አበባው።
የሣውዲ አረቢያ መንግስት “ከሃገሬ ውጡልኝ” ቢል እንኳ፤ የስደተኞችን ሰብአዊ ክብር በጠበቀ መልኩ ማስፈፀም ነበረበት ያሉት አቶ አበባው፤ “ነገር ግን ኢትዮጵያውያኑ በፖሊስ እየተገደሉና እንደ አውሬ እየተሣደዱ ነውና በዚህም የሣውዲ መንግስት ተጠያቂ ይሆናል” ብለዋል፡፡ ጉዳዩን አስመልክቶ በተለያዩ የማህበራዊ ድረ ገፆችና መገናኛ ብዙሃን ላይ የሠላማዊ ሠልፍ ጥሪዎችን ጨምሮ የተለያዩ መግለጫዎችን ሲሠጥ የነበረው የሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በበኩላቸው፤ የሣውዲ አረቢያ መንግስት ህገወጥ የሚላቸውን ስደተኞች በህገ ወጥ መንገድ ማሠቃየቱ በምንም መዘዘኛ ተቀባይነት እንደሌለው ገልፀው፤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ደካማነት የሚያረጋግጥና የኢትዮጵያንም ህዝብ የሚንቅ ድርጊት ነው ብለዋል።
የአገራችን ባለስልጣናት ጉዳዩን የተመለከቱበት መንገድ አሣዝኖኛል፤ አሣፍሮኛልም ያሉት ኢ/ር ይልቃል፤ “ጥንታዊ ታሪክና ክብር ካለው ሃገር መሪዎች የሚጠበቅ አይደለም” ብለዋል፡፡ በየአመቱ አንድ ሚሊዮን ስራ አጥ እየተፈጠረ መሆኑን የሚናገሩት ኢ/ር ይልቃል፤ ወጣቱን ለስራ ፈጣሪነት የሚጋብዝ ነገር አለመኖሩ አንድ የስደት መንስኤ ነው ብለዋል፡፡ “የተማረና አቅሙ የፈቀደ በቦሌ ይሄዳል፤ ያልተማረው ደግሞ ውሃ ይብላኝ እያለ በረሃ እያቋረጠ ይሄዳል” የሚሉት ኢ/ር ይልቃል፤ “አገር እያደገች ዜጐች ስደትን ይመርጣሉ የሚለው የባለስልጣናት አባባል ውሸት ነው” ይላሉ፡፡ የሣውዲ አረቢያ መንግስት በዜጐች ላይ የፈፀመው አሠቃቂ ድርጊት ሳያንስ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናትና የመንግስት ሚዲያ ለጉዳዩ የሠጡት አናሣ ትኩረት አሳዝኖኛል ብለዋል – የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር፡፡ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ዜጐቻችን ሲሰቃዩና የሰው ህይወት ሲጠፋ፣ መንግስት ለጉዳዩ በቂ ትኩረት አልሰጠም የሚሉት ኢ/ር ይልቃል፤ የኢትዮጵያ እና የሣውዲ አረቢያ መንግስት በእኩል ደረጃ ተጠያቂ ናቸው ብለዋል፡፡
የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በበኩላቸው፤ ፓርቲያቸው ጉዳዩን በአፅንኦት እየተከታተለው መሆኑን ገልፀው፤ በሳውዲ የተፈፀመው ተግባር በእጅጉ የሚያሣፍር እና የሚያሣዝን ነው ብለዋል። ማንኛውም ሃገር የራሱን ህግና መመሪያ ሊያወጣ ይችላል ያሉት ዶ/ር ነጋሶ፤ ይሁን እንጂ “ፍቃድ አላሣደሡም” በሚል ሰበብ ዜጐቻችን የሠው ልጅን ክብር በሚያዋርድ ሁኔታ ለስቃይ መዳረጋቸው ብሄራዊ ሃፍረት ነው ብለዋል። ድርጊቱን በፈፀሙት አካላት ላይ ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑን ዶ/ር ነጋሶ ጠቅሰው፤ የሣውዲ አረቢያ መንግስትና የፖሊስ ሃይሉ በህግ ሊጠየቅ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
“አሁን ግን በዜጐቻችን ላይ እየተፈፀመ ባለው ድርጊት የአገራችን ሉአላዊነት ተነክቷል፤ የኢትዮጵያ መንግስትም ይህን የማስጠበቅ ሃላፊነቱን በአግባቡ እየተወጣ አይደለም” ብለዋል ዶ/ር ነጋሶ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ጠበቅ ያለ አቋም መውሠድ እንዳለበትና ዜጐች ደህንነታቸው ተጠብቆ ወደ ሃገራቸው እንዲገቡ በአስቸኳይ መፍትሔ መስጠት እንዳለበትም አሣስበዋል፡፡ የመልካም አስተዳደር እጦት፣ ስራ አጥነትና የመሣሠሉት ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች የሃገሪቱን ዜጐች ለስደት እየዳረገ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ነጋሶ፤ መንግስት ድክመቱን እንዲያሻሽል ሁሉም ዜጋ ግፊት ማድረግ አለበት ብለዋል፡፡
addisadmass
posted by Daniel tesfaye

Saturday, November 9, 2013

"ለወገኖቻችን ዛሬ ነገ ሳንል እንድረስላቸው"

በስቃይና በመከራ ሂወታቸውን እያጡ ና ለከባድ አደጋ እየተጋለጡ ላሉ ወገኖቻችን ዛሬ ነገ ሳንል እንድረስላቸው!!
ይሄ ክፉ መንግስት ለ2 ዓስርት ዓመታት ወገኖቻችንን በተለያይ መንገድ ለስደት ሲዳርጋቸው፥ ሂወታቸው  በረሃ ውስጥ እንደ ቅጠል ወድቀው መቅረታቸው አልበቃ ብሎ፥ እንድሁም በየ ባህር ዳረቻው በየቀኑ የሞት ቁጥራቸው ከፍ በማለቱ ምክንያተ የዓለም የሚድያ መነጋገርያ ዕርስ ሆነው ሰንብተዋል።


ወገኖቻችን እንደዋዛ እየተቀጠቀጡ ሲገደሉ ማንም አቤት የሚል ጠፍቶ ፥ የሚደርስላቸው በማጣት ብቻ  እንደ ቀላል በየቦታው    ሂወታቸውን ማጣታቸው  አልበቃ ብሎ ፥
በየ አረብ አገራት ሴት እቶቻችን ላይ በተለያዩ ችግሮች ምክነያት አካላቸው እና ፥ስነልቦናቸው ተጎድቶ መታከም ባለመቻላቸው ምክንያት እራሳቸው ላይ ሞት እየፈረዱ ወተው የቀሩትን፤ ያልጋ ቁራኛ በመሆን ስሚ አተው እየተስቃዩ አልጋ ላይ ሆነው  የሚያሰሙትን የድረሱልኝ ጥሪ ሰምተን ይሄንን ስቃያቸዉን ለመታደግ ምንን  እያደረግ ነው ያለው ??


 ከሰሞኑነ በህጋዊነት  ሳውዲ የገቡትን፥ ፈጣሪ በአምሳሉ የፈጠረው የስው ልጅን እነሱ በእንሳት እየመሰሉ በሰው ልጅ ሳይሆን በአዉሬ ላይ እንኳን የማይደርግ ተግባር እየፈጰሙ ፥ወገኖቻችንን  ለስቃይ እየዳረጉ ይገግኛሉ።
አንደዚ አይነት ኢሰባዊ ተግባር የዓለም እዝብ አንዲያውቀው እና በተለያዩ መንገዶች የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኙ የየበኩላችንን አላፊነት የመወጣት ግዴታ አለብን ፥ በስቃይና በመከራ ሂወታቸውን እያጡና ለከባድ አደጋ እየተጋለጡ ላሉ ወገኖቻችን ዛሬ ነገ ሳንል እንድረስላቸው።ራሄል ኤፍሬም


Friday, November 8, 2013

ሰበር ዜና – የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ከፍተኛ የአመራር አባላት ላይ ታቅዶ የነበረ የመግደል ሙከራ ከሸፈ


ሰበር ዜና – የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ከፍተኛ የአመራር አባላት ላይ ታቅዶ የነበረ የመግደል ሙከራ ከሸፈ
HOME » መግለጫ / PRESS RELEASE » ሰበር ዜና – የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ከፍተኛ የአመራር አባላት ላይ ታቅዶ የነበረ የመግደል ሙከራ ከሸፈ
NOV 8, 13 • BY  • 

GPF_Logo-Small

የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ከፍተኛ የአመራርአባላት ላይ ታቅዶ የነበረ የመግደል ሙከራ ከሸፈ።
በጠቅላይ ሚንስትር ተብየው ሃይለማሪያም ደሳለኝ እውቅናና ትእዛዝ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል ታጋዮች በሚገኙበት ቦታ ድረስ በመሄድ አመራሩን ለመግደል ሙከራ ቢደረግም ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት በሕዝባዊ ሃይሉ መረጃና ደህንነት ክፍል ከፍተኛ ክትትል ሙከራው መክሸፉን ሕዝባዊ ሃይሉ ገለጸ። ይህ ልዩ ትእዛዝ ጥቅምት 30 2006 ዓ/ም ተፈጻሚ እንዲሆን እቅድ የነበረ ቢሆንም ሕዝባዊ ሃይሉ ጥቅምት 27 2006 ዓ/ም ሊያከሽፈው ችሏል። ዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን።

Wednesday, November 6, 2013

Abbay dam will be owned by Egypt and Sudan

November 5, 2013

Egypt, Sudan, and Ethiopia are all committed to coordinating and cooperating in dealing with Ethiopia’s Grand Renaissance Dam, said Egypt’s Ministry of Irrigation and Water Resources on Monday.
lue Nile River in Guba, Ethiopia, during its diversion
A picture taken on 28 May 2013 shows the Blue Nile River in Guba, Ethiopia, during its diversion (AFP/File, William Lloyd-George)
Egyptian Minister of Irrigation and Water Resources Mohamed Abdel Moteleb said that it was “time to consider a new strategy for the available investment opportunity,” adding that any matter dealing with the dam must be agreed upon by the governments of the three countries.
The countries’ water ministers began meetings in the Sudanese capital of Khartoum on Monday in order to review recommendations put forth by a report formed by a tripartite committee investigating the impacts of the dam on Ethiopia’s neighbours in the north.
Abdel Moteleb added that trilateral support for the dam could set a “good example for cooperation in the region,” adding that he hoped that the outcome of the process would be the “beginning of a new era of cooperation between the three countries.”
“I would like to recall the initiative put forth by the Prime Minister of Ethiopia, a proposal considering the Renaissance Dam a joint regional project from which the three countries could benefit,” said Moteleb in his Monday address to the representatives from the three countries.
Last week Egyptian Minister of Foreign Affairs Nabil Fahmy stressed the importance of joint action and cooperation between countries when dealing with Ethiopia’s dam, saying that the water issue must not be dealt with as a “zero-sum game.”
Spokesman of the foreign ministry Badr Abdelatty said that the Prime Minister of Ethiopia Hailemariam Desalegn would come to Cairo “soon.”
“We will continue dialogue with Ethiopia and our Sudanese brothers,” added Abdelatty.
Source: Daily News

Tuesday, November 5, 2013

International Commission of Jurists (ICJ): Ethiopian Leaders to Face a Trial for Genocide



















October 30, 2013
by Betre Yacob
The International Commission of Jurists (ICJ) reported to have begun to work to bring Ethiopian authorities to justice for having committed a genocide in the Ogaden region. The International Commission of Jurists is a known international human rights organization composed of jurists (including senior judges, attorneys, and lawyers). The commission is known for its dedication to ensuring respect for international human rights standards through the law.

The report came right after different Swedish TV channels showed a movie smuggled out from Ogaden by an Ethiopian refugee, who had been a government official in the region. The 100 hours long movie is said to have many evidences of genocide committed by the Ethiopian government in the region.

Speaking to journalists, Stellan Diaphragm, the commissioner of the Commission, said that he would do everything necessary to bring the case to the International Criminal Court (ICC).

Reports indicate that although Ethiopia is not a member of the ICC, the country can possibly face trial for crimes under international law.

The Ogaden region is a territory in Eastern part of Ethiopia, and populated mainly by ethnic Somalis. Since 2007, the region has been a site of brutal struggle between the government troops and the Ogaden National Liberation Front (ONLF), a rebel group seeking for more autonomy for the region.

Different human right organizations accuse the Ethiopian government of committing grave human right violation (including genocide) against the civilians in attempt to control the ONLF’s public support.

According to the Genocide Wach, the crimes committed in the region include extrajudicial killings, arbitrary detention, rape, torture, disappearances, the destruction of livelihood, the burning of villages and the destroying of life stock.

source: ECADF

Ethiopian man lynched to death in South Africa

A group of men savagely beaten up and killed an Ethiopian man in Mpumalanga, South Africa, last Monday. The gruesome attack took place in broad day light while many people watched, according to the police. The identity of the victim has not been released yet. The police only said that he is a 30-year-old immigrant from Ethiopia.
 Ethiopian attached in South Africa

.