Monday, August 4, 2014

ኃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች አሜሪካ ከመግባታቸው በፊት የኢቦላ ቫይረስ እንደሚመረመሩ ተገለጸ

 ሰሜን አሜሪካ ከነገ ጀምሮ በሚደረገው ትልቅ ስብሰባ ላይ የሚሳተፉ ኃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ የአፍሪካ መሪዎች ስብሰባው ውስጥ ከመግባታቸው አስቀድሞ ከኢቦላ ቫይረስ ነፃ መሆናቸውን ምርመራ እንደሚያደርጉ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ አስታወቁ።

Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn speaks during an interview with Reuters inside his office in the capital Addis Ababa
ከ729 ሰዎች በላይን የገደለውና በርካቶችን በቫይረሱ ተጠቂ ያደረገው ኢቦላ በአሁኑ ወቅት የታማሚዎች ቁጥር ከ 1 ሺህ 200 በላይ እንደሚሆንና ቫይረሱም ከአገራቱ አልፎ በስፋት በመሰራጨት የአህጉሪቷ ብሎም የዓለም ስጋት ሊሆን እንደሚችል ባለሙያዎች የሰጡትን አስተያየት በመጥቀስ ሲኤን ኤን መዘገቡ አይዘነጋም።
በጊኒ፣ በሴራሊዮን እና ላይቤሪያ በርካቶችን እየፈጀ ያለውና የአፍሪካም ትልቁ ስጋት እንደሆነ የሚነገርለት ይኸው በሽታ ወደ ስሜን አሜሪካ እንዳይሰራጭ መንግስታቸው በሰፊው እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወቁት ባራክ ኦባማ ይህ ለ3 ቀናት በዋሽንግተን ዲሲ የሚደረገው በዚህ ትልቅ ስብሰባ ላይ ከ50 በላይ የአፍሪካ መሪዎች የሚገኙ ሲሆን ሁሉም የኢቦላ ምርመራ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

ይህ ሰሚት (ስብሰባ) ነገ ኦገስት 4 ተከፍቶ ኦገስት 6 ቀን 2014 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሲዲሲ የተባለው የአሜሪካ የጤና ተቋም ባለፈው ሰኞ በሰጠው መግለጫ፣ በአገሪቱ ይህ ነው የሚባል የኢቦላ ወረርሽኝ ስጋት እንደሌለ አረጋግጧል፡፡ ይህም ሆኖ ግን በሽታው አደገኛ በመሆኑ መጠንቀቅ ይበጃል ብሏል ተቋሙ፡፡ በሽታው ከተከሰተባቸው የአፍሪካ አገራት የሚመጡ መንገደኞችን ወደ አሜሪካ አለማስገባት ሁነኛ መከላከያ መላ ነው ይላሉ- የሲዲሲ ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት ዶ/ር ማርቲ ሴትሮን፡፡ በቅርቡ ከእነዚያ አገራት የመጡና የኢቦላ ምልክቶች የተሰሟቸው ሰዎችም፣ ዛሬ ነገ ሳይሉ በአፋጣኝ ወደ ህክምና መሄድ እንደሚኖርባቸው ዶክተሩ መክረዋል፡፡ በአገራቱ የሚኖሩ ዜጎችም፣ የበሽታውን መተላለፊያ መንገዶች ጠንቅቀው በመረዳት ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተናግረዋል፡፡
  • 532
     
    EmailShare
(ዘ-ሐበሻ)

Saturday, August 2, 2014

በዋሽንግተን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሊኢ ህ አ ዴ ግ ባለስልጣናት አንመችም አሉ..


non_pulsating_econ_caption

ይቺ አባባል ራሷ ቀላል ተመቸችኝ እንዴ፤ ትላንት በዋሽንግተን ዲሲ በአንዱ ምግብ ቤት ደረታቸውን ነፍተው ሊበሉ ሊጠጡ ተከስተው የነበሩት የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔ አንዳች ጫን ያለ ነገር ገጥሟቸው፤ ሳይበሉ ሳይጠጡ ጎንበስ ብለው እንደወጡ ተሰማ፤
ባለስልጣኑ የገጠማቸው ነገር ሳይወዱ በግዳቸው ልክ ልካቸውን መስማት ሲሆን፤ ይህንን ያደረጉ የዲሲ ወጣቶች የ ኢ ህ አ ዴ ግ ባለስልጣናት በተገኙበት ቦታ ሁሉ፤ በህዝብ ምግብ ቤትም ይሁን በህዝብ መጽዳጃ ቦታ እየጠበቁ ልክ ልካቸውን መንገር እና የሁላችንም ሃላፊነት ነው ሲሉ ይናገራሉ።
ይህንን ማድረግ ፋይዳው ምንድነው… ሲል እሳት የላሰው የኢሳት ጋዜጠኛ መሳይ ከበደ በጠየቃቸው ጊዜም፤ ”እነርሱ በኢትዮጵያ ላሉ ወንድሞቻችን አልመች እንዳሉ ሁሉ እኛም እንርሱን ምቾት መንሳት ዋናው አላማችን ነው” ሲሉ መልሰውለታል።
የኢ ህ አ ዴ ግ ባለስልጣናት ባለፈው ጊዜ በአቶ መልስ ላይ የደረሰውን ነገር ረስተውታል መሰለኝ ሰኞ በአሜሪካ ዋሽንግተን ለአንዳች ስብሰባ ልዑካን ልከዋል አሉ። ዘንድሮ ደግሞ ማን ደንግጦ ሊሞት ይሆን እያልን እየተጨነቅን ባለበት በዚህ ሰዓት የዲሲ ወጣቶች ለባልስልጣኖቹ ኮረኮንች መንገድ ሆነው አልመች ብለዋቸዋል። (ባለስልጣኖቹም ምን አለኝ ኮብል ስቶኔ… እያሉ መስሪያ ቤታቸውን እና መሳሪያ ታጣቂዎቻቸውን እየናፈቁ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው)
በዚህ አጋጣሚ ሰኞ በዋሽንግተን እና አካባቢዋ ይሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለስልጣኖቹ ላይ የተቃውሞ ቁጣቸውን ለማሰማት ተቀጣጥረዋል። ባለስልጣኖቻችን እንግዲህ ቆፍጠን ነው! ብለን እንምከር ወይስ ይቻሉት…! ?

Tuesday, July 22, 2014

የጤና ባለሞያዋ ወይዘሪት ተክለ ደስታ ከስራ ተባረረች።

  • 551
     
    EmailSha
ethsat

               የታዋቂው ፖለቲከኛና ጸሃፊ አብርሃ ደስታ እህት ከስራ ታገደች

ሐምሌ ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአረና የወጣው መረጃ እንደሚያሳየው ወይዘሪት ተክለ ደስታ የኣብራሃ ደስታ እህት በመሆንዋ ብቻ ከስራዋ ታግዳለች ።

 ወይዘሪት ተክለ ደስታ የጤና ባለሙያ ስትሆን የህወሓት ኣባልና የራያ ዓዘቦ ወረዳ የጤና ፅህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ ሁና ታገለግል ነበር።የወረዳው ባለስልጣናት “አንቺ እንደ ወንድምሽ ዓረናነሽ ፣ ላንቺ የሚሆን የህወሓት ሃላፊነትም ይሁን የሞያ ስራ የለንም፣ ላንቺ እንኳን ስራ፣ መሬቱም እሳት ሆኖ ያቃጥልሻል ” በማለት ከስራዋም ከህወሃት አባልነትም እንዳባረሩዋት ድርጅቱ አስታውቋል።

የህወሓት ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ኣባይ ወልዱ ታላቅ ወንድም የሆነው ኣቶ ኣውዓሎም ወልዱ የዓረና መስራችና ኣመራር ኣባልነው።ይህ በእንዲህ እንዳለ ወይዘሮ ኣልጋነሽ ገብሩ በህወሓት መንግስት “ኣሸባሪ” ተብላ ከተከሰሰች ጀምሮ 3ቱ ህፃናት ልጆቿ የጎዳና ሂወት መምራት መጀመራቸውን ከድርጅቱ የተገኘው መረጃ አመልክቷል።ህፃናቱ ኣባታቸውን  ከ9 ዓመት  በፊት  በሞት  ያጡ  ሲሆኑ፣  ጠላ እየጠመቀች ታስተዳድራቸው የነበረችው እናታቸውን በእስር ምክንያት ካጡ ብሗላ ትምህርታቸው ኣቋርጠው ፣የጎዳና ሂወት መግፋት ጀምረዋል።

እናታቸው  በ”ኣሸባሪነት” ተፈርጃ  በእስር ያጡ  ህፃናትን ለመንከባከብ በህብረት ባንክ መቐለ ቅርንጫፍ በ202 041 606 379 3018 የሚልየአካውንት ቁጥርተከፍቷል።
የሂሳብ ደፍተሩ የተከፍተው በወይ ዘሮ ኣልጋነሽ ታናሽ እህት ወይዘሮ ፅጌ ገብሩነው።

Thursday, July 3, 2014

(Breaking News) Dr. Brehanu Nega Speaks After Yemen handed over Andargac...

(ሰበር ዜና) የየመን መንግስት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አሳልፎ ሰጠ

andargachew
  • 685
     
    EmailShare

) የደረሰን ዜና እንደሚያመለክተው፣ የግንቦት ሰባቱ ዋና ጸሃፊና የድርጅቱ ሞተር የሚባሉት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ  ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፈው ተሰጥተዋል። አቶ አንዳርጋቸው ለትራንዚት ሰንዓ የመን በቆዩበት ጊዜ በየመን ደህንነት ሃላፊዎች  ከአሥር ቀናት በፊት የታገቱ ሲሆን፣ ድርጅታቸው ግንቦት ሰባት እርሳቸዉን ለማስፈታት ዉስጥ ዉስጡን በርካታ ጥረቶች ሲያደርግ እንደቆየም ከድርጅቱ የወጣዉ መግለጫ ይጠቁማል።
አቶ አንዳርጋቸውን ለመጎብኘት ጥረት ያደረገው የእንግሊዝ ኤምባሲ፣ በየመን አቶ አንዳርጋቸውን ለማግኘት እንዳልቻለ የገለጸዉ የደረሰን ዘገባ፣ አቶ አንዳርጋቸው ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፈው የተሰጡት፣ በየመን መንግስት መያዛቸው በድርጅታቸው ለሕዝብ ይፋ ከመሆኑ በፊት እንደሆነም ለማረጋገጥ ችለናል።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከግንቦት ሰባት አባላት ዉጭ በበርካታ ኢትዮጵያዉያን ዘንድ በቆራጥነታቸውና ሐሳብ አመንጪነታቸው የሚታወቁ ናቸው። በምርጫ ዘጠና ሰባት ወቅት ፣ በቅንጅት ዉስጥ ትልቅ ተሳትፎ ያደርጉ የነበሩት አቶ አንዳርጋቸው፣ ለሰላማዊ ትግሉም መጽሃፍ ጽፈው ያበረከቱ አገር ወዳድ ሰው ናቸው። በወቅቱ የኢሕአዴግ መንግስት አቶ አንዳርጋቸውን በዝዋይ አስሮ የነበረ ሲሆን፣ በዚያም በደረስባቸው ድብደባ አይናቸው ላይ ጉዳት እንደደረሰም በወቅቱ መዘገቡ ይታወሳል። አቶ አንዳርጋቸው አገዛዙ በሰላም አይወርድም በሚል ሁለገብ ትግል አደርጋለውሁ የሚለው የግንቦት ሰባት ከፍተኛ አመራር አባል ሆነው ሲሰሩ የነበሩ ታጋይ ናቸው።

Tuesday, July 1, 2014

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ

          


የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። እንዲያውም የየመን ባለስልጣናት አምባገኑን ወያኔ ለመርዳት ባለው ፍላጎት ሳቢያ መሪያችንን አሳልፎ ሊሰጠው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮብናል።http://www.ginbot7.org/wp-content/uploads/2013/05/g7-logo.jpg

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን፣ እውቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ፤ ዝግጁነቱንም በተግባር ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። የየመን መንግሥት ከዘረኛውና ፋሽስታዊው ወያኔ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ታጋይ መሪያችን ላይ እየፀመ ያለውን ደባ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅ የንቅናቄዓችን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ወስኗል።
ትግላችን መስዋትነት እንደሚያስከፍል እናውቃለን። ከዚህ በፊትም ብዙ ጓዶቻችን መስዋዕትነት ከፍለዋል፤ ወደፊትም ብዙ መስዋዕትነት መከፈሉ የማይቀር ጉዳይ ነው። አሁን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የደረሰውና ወደፊትም ሊደርስ የሚችለው ጉዳት ምሬታችን በማብዛት፣ ቁጣችንና ዝግጁነታችን ከማጠንከር በስተቀር ቅንጣት ታክል እንኳን ወደ ኋላ እንድናፈገፍግ እንደማያደርገን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለአባሎቻችንና ለደጋፊዎቻችን ሁሉ መግለጽ እንወዳለን።

መንግሥታት ይመጣሉ፣ ይሄዳሉ። ኢትዮጵያና የመን ግን ጎረቤታሞች ሆነው መቆየታቸው የማይቀር ነው። የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም። በዚህም ምክንያት የየመን መንግሥት የሁለቱን አገሮች ሕዝቦች የቆየ ወዳጅነት የሚያደፈርስ እርምጃ ወስዷል። የየመን መንግሥት የየመንን የወደፊት የረዥም ጊዜ ጥቅም እንዲያሰላና ያገተብንን መሪ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንመክራለን። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በመሪያችን ላይ ጉዳት ቢደርስ ወይም ለወያኔ አሳልፎ ቢሰጥ የመን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የማይሽር ቂም ውስጥ የምትገባ መሆኑን የየመን መንግሥት አውቆ በጥብቅ እንዲያስብበት እናስጠነቅቃለን።
በየመን መንግሥት አልሰማ ባይነት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለፋሽስቱ የወያኔ አገዛዝ ተላልፎ ቢሰጥ በአካሉና በሕይወቱ ለሚደርሰው ሁሉ የወያኔ ፋሽስቶችን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑ ከአሁኑ እናስጠነቅቃለን። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስና ሕይወት ላይ የሚደርሰው ማንኛውም ጥቃት ለነፃነታቸው ለመሰዋት ዝግጁ የሚሆኑ እልፍ አዕላፍ ታጋዮችን እንደሚፈጥር ጥርጥር የለንም። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስ እና ሕይወት ላይ ለሚደርሰው ጥቃት ሁሉ በማንኛውም መንገድ በማንኛውም ቦታ የምንበቀል መሆኑንና ብዙ የወያኔ ሹማምንት ዋጋ የሚከፍሉበት እንደሚሆን እንዲያውቁት እናስጠነቅቃለን ።