Saturday, May 16, 2015

በስቶክሆልም በሊቢያ ሕይወታቸውን ያጡ ኢትዮጵያውያን በደመቀ ሁኔታ ታስበው ዋሉ




ንኤል ሐረር ለዘ-ሐበሻ ከስዊድን እንደዘገበው:- 
ትላንት ሐሙስ ግንቦት 6/2007 በምስራቅ አፍሪካ እና አውሮፓ አህጉረ ስብከት የመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ እስቶኮልም ሆተርየት ባዘጋጀው የ21ኛው ክፍለ ዘመን ድንቅ የእግዚአብሔር ምስክሮች ለሆኑት 30 (ሰላሳ ) የኦርቶዶክስ ልጆች መታሰቢያ ፕሮግራም በዕለቱ ከተገኙ የግብፅ የሶርያ ብጹአን አባቶች ጋር በደማቅ ሁኔታ ታሥቦ ውሏል፡፡ 

በዕለቱ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን ካህንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ካህናት ተገኝተዋል። እንዲሁም በስቶኮልም ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ስንበት ት/ቤት ተማሪዎች የህብረት መዝሙረና በወቅቱ የነበረውን የሰማዕታቱን ጽናት የሚያሳይ ትዕይንት ፤የአበባ ማስቀመጥ እና የጧፍ ማብራት ፕሮግራሞ ተካሂዷል። 

No comments:

Post a Comment