Monday, April 7, 2014

አገራችን ምን አይነት ምስቅልቅል ውስጥ እንደሆነች ለማንም ማስረዳት አስፈላጊ አይደለም።

በዋሽንግተን ዲሲ የሽግግር ምክርቤቱ አመራርm ስብሰባ

ውድ ኢትዮጵያውያን፤

አገራችን ምን አይነት ምስቅልቅል ውስጥ እንደሆነች ለማንም ማስረዳት አስፈላጊ አይደለም። ከዚህም አልፎ ተዘጋጅተንና አቅደን ካልጠበቅነው መጭው ስርአት ተመሳሳይ ወይም ከዚህኛው የከፋ ይሆናል ብለን ሁላችንም እንሰጋለን። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሽግግር ምክር ቤት ይህንን የዝግጅት አስፈላጊነትን ጽንሰ ሀሳብ ለህዝብ በአንክሮ ካስገነዘበ ወዲህ ዛሬ ይህ አጀንዳ በተቃዋሚ ድርጅቶች፤ በተለያዩ ተቋማት እንዲሁም በመላው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ዘንድ የመወያያ ርእስ ሆኗል።  

በመጭው እሁድ ሚያዝያ 5 (April 13, 2014) ባዘጋጀነው ስብሰባ የተለያዩ የማህብረሰባችን ተወካዮች በዚሁ አንገብጋቢ ጉዳይ ላይ ንግግር ያደርጋሉ ከህዝብም ጋር ይወያያሉ። ይህ ስብሰባ የተሳካ ለማድረግ በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ የሚገኙ ጓደኞችዎንና ዘመድ ወዳጆችዎን በመጋበዝና እራስዎም በመገኘት የድርሻዎን ያበርክቱ ዘንድ በትህትና እንጠይቃለን። ስለስብሰባው በይበልጥ ለማወቅ፤ ከዚህ ኢሜይል ጋር ተያያዥ ሆኖ የተላከውን በራሪ

ወረቀት ይመልከቱ።

የሽግግር ምክርቤቱ አመራር

No comments:

Post a Comment