Saturday, December 28, 2013

በዓለም ደረጃ «ደካማ» የሚባሉ የዓለማችን ዜጎች «ጠንካራ» በሚባሉት ቅኝ ገዢዎች ላይ አንፀባራቂ ድል ማስመዝገብ እንደሚችሉ እርሣቸው የመሩት የዐድዋውድል ሕያው ምሥክር ነው።

የአኖሌ ሐውልት ጉዳይ … «አሣ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል» እንዳይሆን

moresh-logoበቅርቡ የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ በሚቆጣጠረው የቴሌቪዥን ጣቢያ አንድ ዝግጅት ቀርቦ ነበር (ምንጭ፦ http://www.youtube.com/watch?v=ejucti17fAU)። የዝግጅቱ ትኩረትም «የዳግማዊ አፄ ምኒልክ ሠራዊት በአርሲ እናቶች ላይ በፈፀመው የጡት መቁረጥ ግፍ» መታሠቢያ የሆነ ሐውልት ስለመቆሙ ነበር። «ነገርን ከሥሩ ፣ ውኃን ከጥሩ» ይባላልና ለመሆኑ የዚህ አዲስ ሐውልት ባለቤቶች እነማን ናቸው? በሐውልቱስ መቆም ማን ምን ፋይዳ ያገኝበታል? ብሎ መጠየቁ ተገቢ ይሆናል።
ከታሪክ እንደምንገነዘበው ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ነገሥታት ውስጥ እጅግ ከፍተኛ ታሪካዊ ተግባሮችን ያከናውኑ ከሚባሉት ጥቂቶች መካከል የሚመደቡ ናቸው። የኢትዮጵያን አንድነት በማጠናከር ረገድ ከአፄ አምደጽዮን ወዲህ የተነሡት ትልቁ አገር ገንቢ ናቸው። በዚህ አኳያ የላቀ ድርሻ ያላቸው ምናልባትም ከዚያ በፊት እነ አፄ ካሌብ እና አፄ ኢዛና (አብርሃ) ናቸው። ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ወደ ኢትዮጵያ በማስገባት ደረጃ ኮትኩተው ካሣደጓቸው ከዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የላቀ ስኬት ለማስመዝገብ ብልህነቱም ሆነ መልካም አጋጣሚው ነበራቸው። ከሁሉም በላይ በጥቁር አፍሪቃ ብቻ ሣይሆን በዓለም ደረጃ «ደካማ» የሚባሉ የዓለማችን ዜጎች «ጠንካራ» በሚባሉት ቅኝ ገዢዎች ላይ አንፀባራቂ ድል ማስመዝገብ እንደሚችሉ እርሣቸው የመሩት የዐድዋው ድል ሕያው ምሥክር ነው። ስለዚህ እኒህን ሁሉ ታላላቅ ተግባሮች ባከናወኑ ንጉሠ ነገሥት ላይ ይህ ሁሉ ውርጅብኝ እና ስም ማጉደፍ በእነማን ፣ ለምን ተብሎ እንደሚካሄድ አብጠርጥሮ ማሣወቅ ያስፈልጋል።
ለመሆኑ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ማን ነበሩ? ዳግማዊ አፄ ምኒልክ የሸዋው ንጉሥ የኃይለመለኮት ሣህለሥላሤ እና የወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያቦ ልጅ ናቸው። በአባታቸው ወገን ኢትዮጵያን ከቀዳማዊ ምኒልክ ጀምሮ ያስተዳደረው የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥት ደም ያላቸው ሲሆን እናታቸው ደግሞ ከጉራጌ ነገድ የሚወለዱ ናቸው። በእናታቸውም ሆነ በአባታቸው ወገን ያለው ዝርዝር የትውልድ ሐረጋቸው በደንብ ቢጠና ከሁለት በላይ ከሆኑ ነገዶች ቅይጥ ዘር እንደሚኖራቸው እሙን ነው። በዚህ ጽሑፍ ደረጃ ለማስተላለፍ የሚፈለገው ሃቅ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ቢያንስ ከሁለት የኢትዮጵያ ነገዶች የተገኙ እንጂ የዘመኑ ዘባራቂዎች በሐሰት እንደሚደልዙት «የዐማራ ንጉሠ ነገሥት» አልነበሩም። እርሣቸውም በየትኛውም አጋጣሚ ራሣቸውን በእንደዚህ ዓይነት መጠሪያ ገልፀው አያውቁም።MWAO_V2No7_አርብ ታኅሣሥ ፲፰ ቀን ፪ሺህ፮ ዓም_(Fr 27 Dec 2013)_የአኖሌ ሐውልት ጉዳይ-አሣ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል-እንዳይሆን Read in pdf.

Esat special Public meeting in Bergen Norway part 1 Dec 2013

http://ethsat.com/video/esat-special-public-meeting-in-bergen-norway-part-1-dec-2013/

Friday, December 27, 2013

Amnesty International: Will you help free her husband?

Amnesty International UK

Eskinder Nega has been sentenced to 18 years in prison for telling the truth. Will you help us to secure his release and return him to his family?
By making a donation today you will support our campaign to get Eskinder home to his family and his vital work as a journalist. Click here
In this video, Eskinder’ wife Serkalem, talks about the pain both her and their son are going through being separated from Eskinder.
When the Ethiopian government used anti-terror laws to silence its critics, Eskinder spoke out in protest. As a result he was arrested for the eighth time and sentenced to 18 years in prison.
Despite the lies and the pain of separation from his wife and son, Eskinder’s hope for the future of Ethiopia and its people is as strong as ever. In a letter smuggled out of prison he said:
‘Freedom is partial to no race. Freedom has no religion. Freedom favours no ethnicity. Freedom discriminates not between rich and poor countries. Inevitably, freedom will overwhelm Ethiopia.’
What we are doing
To help free Eskinder we are mobilising our worldwide network to take action in support of his release. Over 20,000 people in the UK have already joined the campaign by writing letters, sending cards or signing the global petition.Eskinder' wife Serkalem, talks about the pain both her and their son
We are also lobbying Prime Minister Hailemarian Desalegn directly, and focusing media attention on Eskinder’s case and the worsening crackdown on free speech and freedom of expression in Ethiopia.
This is the same kind of campaigning that in 2010 helped secure the release of Eskinder’s friend, Birtukan Mideksa
She was serving a life sentence when the Ethiopian government set her free thanks to pressure from Amnesty International.
We know we can get Eskinder home. Help us do it!

በጎንደር ዳባት ሕጻን ሰለሞን ላይ ማን የጥይት እሩምታ አወረደበት?



ከዳዊት ሰለሞን
ሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ ነዋሪ የነበሩት የ55 ዓመቱ አቶ ማስረሻ ጥላሁን የተመሰከረላቸው አርሶ አደር ገበሬ በመሆናቸው የክልሉ ግብርና ጽ/ቤት ሞዴል አርሶ አደር በማለት ሸልሟቸዋል፡፡የሁለት ወንድና የአምስት ሴት ልጆች አባት የሆኑት አቶ ማስረሻ ወሰኔን ገፍተሃል የሚል ክስ ቀርቦባቸው በዳባት ፍርድ ቤት 300 ብር መቀጮ ተጥሎባቸው በመክፈል ወደ እርሻቸው ቢመለሱም የገበሬ ቀበሌ ማህበሩ ሊያስቀምጣቸው አልቻለም፡፡
ጥቅምት 15/2006ዓ.ም ከሁለተኛ ልጃቸው ሰለሞን ማስረሻ ጋር አትክልት ተክለው አመሻሹ ለይ ተዳክመው መኖሪያ ቤታቸው ገብተዋል፡፡ማለዳ 12፡00 ከመኝታው ባላቋረጠው የውሾች ጩህት ከእንቅልፉ ተነሳው ሰለሞን በሩን ከፍቶ ሲወጣ የጥይት እሩምታ ይወርድበታል፡፡አባት ልጄን ብለው የሌሊት ልብሳቸውን እንደለበሱ ወደ ውጪ ሲወጡ የጥይቶቹ አቅጣጫ ወደ እርሳቸው በመዞሩ ማን እንደተኮሰባቸውና ማን እንደመታቸው ለማየት እንኳን ሳይታደሉ ይህችን ጨካኝ አለም ተሰናበቱ፡፡

መኖሪያ ቤቱ ላይ በሚወርደው የጥይት እሩምታ የተነሳ ሁለት ላሞችና አንዲት ጊደር ተገደሉ፡፡የስምንት አመቷ ስለእናት ማስረሻ ቀኝ እጇ ላይ በጥይት ተመታች፡፡ባለቤታቸውን በሞት የተነጠቁትና ምንም የማታውቀውን ህጻን ልጃቸውን አካለ ጎደሎ ያደረገባቸውን ጥይት ማን እንደተኮሰው ለማወቅ ለዳባት ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ አቤት ሲሉ ‹‹ባለቤትዎ ሽፍታ መረጃ ስለደረሰን ግድያውን የፈጸመው የጸረ ሽብር ግብር ሃይል ነው››ተብለዋል፡፡‹‹ሽፍታ እንዴት ባለ80 ቆርቆሮ ቤት ይሰራል?ልጆቹን ያስተምራል?ሞዴል አርሶ አደር ተብሎ ይሸለለማል?በየት አገር በብአዴን ስብሰባ ላይ እንድትገኝ ተብሎ በደብዳቤ ይጠራል?እንዴት ሽፍታ የመለስ ዜናዊን አደራ ለመወጣት በምንችልበት ሁኔታ ለመወያያት እንድንነጋገር ይባላል? ›› ጥያቄዎቹን ፖሊሶቹ ሊመልሱላቸው ባለመቻላቸው ወደ ክልሉ አስተዳደር አምርተዋል፡፡ክልሉ ለዞኑ ዞኑ ለወረዳው ደብዳቤ እየጻፈ እስካሁን ድረስ የአቶ ማስረሻ እውነተኛ የግድያ መንስኤ መታወቅ አልቻለም፡፡

Wednesday, December 25, 2013

ፋይናንሽያል ትራንስፓረንሲ ኳሊሽን ያወጣዉንና ኢትዮጵያ በህገወጥ የገንዘብ ፍሰት (illicit financial flow) በፈረንጆቹ ከ 2000 እስከ 2009 ያጣችዉን 11. 7 ቢልየን ዶላር ልብ ይሏል::

ኢኮኖሚያችን ሲያድግ የህዝቡ ኑሮ ለምን አሽቆለቆለ?

                                                               

ላለፉት 8 እና ዘጠኝ ዓመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሁለት አሃዝ አያደገ ነው ሲባል እንሰማለን፤  የእድገት ፍጥነቱ  ላይ የሚነሱ በርካታ ጥያቄውች  ቢኖሩም መንግስት  የመንገድ ግንባታ ፣ የኃይል ማመንጫ ግንባታወችን እና መሰል ነገሮችን  በመጥቀስ እድገት እንዳለ አስረግጦ ይከራከራል::  በሌላ በኩል የኢኮኖሚ እድገቱ ተመዘገበ በሚባልባቸው ዓመታት በዋጋ ንረት የህዝቡ ኑሮ ከጊዜ ወደጊዜ እያሽቆለቆለ  እንደሆነ በግልፅ የሚታይ ነገር ነው:: ታዲያ  የኢኮኖሚ እድገት አለ በተባለባቸው ዓመታት የህዝቡ ኑሮ ለምን አሽቆለቆለ? ይህን ጥያቄ ከ 7 ዓመት በፊት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ  ተጠይቀው የሰጡት መልስ የዋጋ ንረቱን የኢኮኖሚ እድገቱ እራሱ የፈጠረው ጉዳይ ነው ነገር ግን ቀስ በቀስ እድገቱ ሲቀጥል ራሱ እድገቱ ችግሩን ይፈታዋል ብለው ነበር፤ ነገር ግን ከሰባት ዓመት በዃላም እንኩአን ሊሻሻል  የህዝቡ የኑሮ ሁኔታ ከቀን ወደቀን እየባሰበት ሂዷል::  ችግሩ የተለያዩ  ምንጮች ቢኖሩትም በዋናነት በ 2 ከፍሎ ማየት ይቻላል::

፩. የኢኮኖሚ እድገቱ ምንጭ
፪. የሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር
የኢኮኖሚ እድገት ማለት በአጭሩ ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ተጨማሪ ሀብት መፍጠር ማለት ነው::  በመጀምሪያ ላለፉት 8  እና ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ ዉስጥ  የተፈጠሩት ተጨማሪ ሀብቶች ምንድን ናቸው ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል ፤  በአብዛኛዉ ሀገሪቱ ዉስጥ የተፈጠሩት ሀብቶች ከመንገድ ፣ ከሕንፃ እና ከ ከኃይል ማመንጫ ከግንባታ ጋር የተያያዙ ናቸው:: በመቀጠልም የዚህ ሀብት የገንዝብ ምንጭ ምንድን ነው ብሎ ማየት ያስፈልጋል፤ የገንዘቡ ምንጭ በዋናነት ከብድር እና እርዳታ የተገኘ ሀብት ነው ፣ በተለይም በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ 1998 ዓም ጀምሮ በሶማሊያ በመጀመሪያ የእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት በመቀጠልም የአልሻባብ እንቅስቃሴ መጠናከር ለኢትዮጵያ ትልቅ ሲሳይ ይዞ ነው የመጣው:: በሶማሊያ ያለዉን ሁኔታ  ለመቆጣጠር ምዕራባዉያኑ የሚያደርጉትን ጥረት በመደገፍ  በዋና አጋርነት የተሰለፈችዉ ኢትዮጵያ ላለፉት ስምንት ዓመታት በየዓመቱ በቢልየን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ በእርዳታ መልክ ከምዕራብ ሃገራት እንድታገኝ አድርጓታል:: ይህም ማለት ሀገሪቱ ዉስጥ የጎላ  የኢኮኖሚያዊ መዋቅር ፣ የአሰራር ስርዓት  እና የቴክኖሎጅ ለውጥ ሳይኖር ከፍተኛ ገንዘብ ወደኢኮኖሚው ፈሰስ እንዲሆን አድርጓል:: በሌላ አገላለፅ  የቆየው የሀገሪቱ  ኢኮኖሚ የጎላ የምርት ጭማሪ ሳይኖረው ከዉጭ የተገኘ ብድር እና እርዳታ ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ተጨመረ እና የኢኮኖሚዉ መጠን አደገ ማለት ነው::  ስለዚህ የህዝቡን የኑሮ ሁኔታ እና የሀገሪቱን ተወዳዳሪነት ሊያሻሽል የሚችል የግብርና እና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ የጎላ  ለዉጥ ሳይታይ ለመሠረት ልማት ኢኮኖሚዉ ዉስጥ ፈሰስ የተደረገው ገንዝብ የገንዘብ አቅርቦትን (Money Supply) በመጨመር እና  የአገልግሎት ዘርፉ ( Service sector) ከሌሎቹ የኢኮኖሚ ዘርፎች ተነጥሎ እንዲለጠጥ እንዲሁም ዋጋ እንዲንር በማድረግ አብዛኛዉን ሕዝብ ለችግር አጋለጠ ::

ከብድር እና እርዳታ የተገኘው ገንዘብ መሰረተ ልማት ላይ ሲዉል ከላይ የተገለፀው ችግር ቢኖርበትም በአንፃሩ የመሰረተ ልማት መስፋፋት የማምረቻ ወጭ ( cost of production) እንዲቀንስ በማድረግ የሚያስገኘው ጥቅም አለ ፤ በተጨማሪም ገንዘብ ገንዘብን ይፈጥራል “ money creats money” በሚለው የኢኮኖምክስ  መርህ መሰረት ኢኮኖሚዉ ዉስጥ የተረጨው ገንዘብ በአብዛኛዉ አገልግሎት ዘርፉ ላይ የፈጠረው ተጨማሪ ሀብት አለ:: ነገር ግን ይህ የተፈጠረ ተጨማሪ ሀብት በጠንካራ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መዋቅር ስላልተመራ ወደጥቂት ሰወች እጅ እንዲገባ ሁኗል::  ሃብቱ እጃቸው የገባ ሰወችም የኢኮኖሚዉን መዋቅር ሊለዉጡ የሚችሉ እንደኢንዱስትሪ አይነት ዘርፎች ላይ ከመሰማራት ይልቅ ከሙሰኛ ባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለዉን የከተማ ቦታ በኢንቨስትመንት እና በሊዝ ስም በመዉሰድ ህንፃ በመገንባት እየተለጠጠ ላለው የአገልግሎት ዘርፍ በማከራየት በአቁአራጭ ከፍተኛ ገቢ ለመሰብሰብ ተጠቀሙበት::

በሌላ በኩል የሀገሪቱ የመሬት አስተዳደር ስርዓት በሙስና የተጨማለቀ እና ወጥ ስላሆነና አዳዲስ ብቅ ለሚሉ ባለሀብቶች መሬት ማግኘት ከባድ ስለሆነ ሀገሪቱ አሁን ባለችበት ተጨባጭ ሁኔታ ወሳኝ ሀብት (strategic resource) የሆነዉን የከተማ ቦታ ቀድመው የያዙ ባለሀብቶች የገቢያ ዉድድሩን ሚዛናዊ እንዳይሆን በማድረግ አዲስ የሚፈጠሩ ተወዳዳሪያቸውን በቀላሉ ከገቢያ ያስወጣሉ:: በተጨማሪም እንደነዚህ አይነቶቹ  ባለሀብቶች በአብዛኛው የፖለቲካዉ እና የግዥዉ ፓርቲ ጥገኛ ስለሆኑ የሚጠበቅባቸዉን ያክል  ግብር እና ታክስ አይከፍሉም:: ሥራቸዉን ስለሚያውቁም በሀገሪቱ በረጅም ጊዜ ሊከሰት ይችላል ብለው የሚፈሩትን ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ስለሚሰጉ የሚያገኙትን ትርፍ ወደዉጭ ያሽሻሉ ፤ በጎን ሙሰኛ ባለስልጣናትም የሚዘርፉትን ገንዘብ ከሀገር ያሸሻሉ:: ከዚህ ላይ ፋይናንሽያል ትራንስፓረንሲ ኳሊሽን  ያወጣዉንና ኢትዮጵያ በህገወጥ የገንዘብ ፍሰት (illicit financial flow) በፈረንጆቹ ከ 2000 እስከ 2009 ያጣችዉን 11. 7 ቢልየን ዶላር ልብ ይሏል::

ለማጠቃለል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ጤናማ ሁኖ እንዲያድግ ከተፈለገ ከላይ የተጠቀሱት  የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ መዋቅር ድክመቶች መስተካከል የሚገባቸዉ ሲሆን ፤ በዉጭ ብድር እና እርዳታ ላይ መንጠልጠሉን ቀንሶ ከሀገር ቤት በፍትሃዊነት ከሚሰበሰብ ግብር ሊሆን ይገባል:: ከዉጭ የሚገኘዉን ሀብትም  በብዛት መሰረተ ልማት ላይ ብቻ ማዋሉ የሚያስከትለዉን ችግር ጥልቅ ጥናት በማካሄድ  መመርመር እና  ገንዘቡ ከመሰረተ ልማቱ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪው እና የእርሻዉን ዘርፍ መዋቅር ወደተሻለ ደረጃ እንዲደርስ ለማስቻልም መሰራት አለበት:: ከሁሉም በላይ ግን የኢኮኖሚ ነቀርሳ የሆነዉን ሙስና ለማስወገድ ከአንድ ፓርቲ የበላይነት ወደ መድብለ ፓርቲ ስርዓት መሸጋገር እንዲሁም ተጠያቂነትን ሊያጠናክሩ የሚችሉ እንደገለልተኛ ፍርድ ቤቶች ፣ የግል መገናኛ ብዙሃን  የመሳሰሉትን ተቋማት መፍጠር ያስፈልጋል:: ይህ ካልሆነ ግን ሀገሪቱ ሽህ ጊዜ ብታድግ የኢኮኖሚውን ፍሬ ጥቂቶች እየበሉ የአብዛኛዉ ሕዝብ  ኑሮ ማሽቆልቆሉ ይቀጥላል::

Tuesday, December 24, 2013

ዳኛው ጥር 10 ያነበቡት በኮምፒውተር ያልተተየበ የእጅ ጽሁፍ ነበር፡፡

ከርዕዮት ዓለሙ ችሎት ጀርባ ያለው ጥቁር ዳኛ ማነው? – የሰነድ ማስረጃ የያዘ ጥብቅ ምስጢር



ከጋዜጠኛ ስለሺ ሐጎስ
ክፍል አንድ
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥር አስር ቀን 2004 ዓ.ም በእነ ርዕዮት አለሙ ላይ ያስተላለፈው የጥፋተኝነት ውሳኔ በችሎቱ የተሰየሙት ዳኞች በነጻ ህሊና የሰጡት ፍርድ ነው ብሎ ያመነ ሰው አልነበረም፡፡ እዚህም እዚያም ሲወራ የነበረው ውሳኔው በመንግስት ፍላጎት ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነበር፡፡ ፕሮፌሰር መስፍንን ጨምሮ በርካታ ሰወች ይህንኑ በአደባባይ ጽፈውታል፡፡ ቆየት ብሎ ግን ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ የሚገልጹና ተጨማሪ ነገር ለማወቅ የሚገፋፉ መረጃዎች ወደኔ መምጣት ጀመሩ፡፡
እርግጥ የኢትየጵያ የፍትህ ስርአት በተደጋጋሚ ተፈትኖ የወደቀና ነጻነቱ ጥያቄ ውስጥ የገባ ከመሆኑ አንጻር እንዲህ አይነት የጥርጣሬ ድምጾች መሰማታቸው በራሱ ብዙ የሚገርም አይደለም፡፡ በመሆኑም በጉዳዩ ላይ የምር እንዳስብ የሆንኩት ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ በመስማቴ ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም ከዚያ በፊት በነበረው የፍርድ ሂደት ያስተዋልኳቸው ሦስት አጠራጣሪ ክስተቶቸ ናቸው እንደ ጋዜጠኛም ሆነ እንደ ርዕዮት የቅርብ ሰው ስለ ጉዳዩ ብዙ ለማወቅ እንድታትር የገፋፋኝ፡፡
የመጀመሪያው፣ ርዕዮት በማዕከላዊ ምርመራ ላይ እያለች የታዘብኩት ነው፡፡ ርዕዮት በተያዘች በማግስቱ አራዳ ፍርድ ቤት ቀርባ ፖሊስ የ28 ቀን የምርመራ ጊዜ ሲጠይቅ አባቷና ጠበቃዋ የሆኑት አቶ አለሙ ደግሞ ቤተሰብ እንዲጠይቃትና የህግ ምክር እንድታገኝ አመለከቱ፡፡ ዳኛዋም ፖሊስ ይህንኑ እንዲፈጽም አዘውና የ28 ቀን የምርመራ ጊዜ ሰጥተው ችሎቱ አበቃ፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ርዕዮት፣ ጠበቃም ሆነ ቤተሰብ ሳታገኝ 28ቱ ቀን አለፈ፡፡
የነበረው አማራጭ የቀጠሮው እለት ጠበቃዋ ገብተው ድጋሜ እንዲያመለክቱ ማድረግ ብቻ ነበር፡፡ እኛም ፍርድ ቤት ስትመጣ ጠብቀን ቢያንስ አይኗን ለማየት ጓጉተናል፡፡ በዕለቱ የሆነው ግን በጣም አስገራሚም አሳዛኝም ነበር፡፡
ቀጠሮው ከሰዓት በኋላ 8 ሰዓት ነበረ፡፡ በዚያን ዕለት ጠዋት 2፡30 ቁርስ ላደርስላት ወደ ማዕከላዊ ስሄድ ከዚያን ዕለት በፊትም ሆነ በኋላ አይቻት የማላውቃት አንዲት ልጅ “ርዕዮትን በሌሊት ወደ ፍርድ ቤት ወስደዋታል ሮጠህ ድረስባት” ብላኝ ካጠገቤ ብን አለች፡፡ ለአቶ አለሙ በስልክ ይህንኑ ነግሬ ወደ ፍርድ ቤቱ አመራሁ፡፡ ቦታው ቅርብ በመሆኑ 10 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ደረስኩ፡፡ እኔ ወደ ግቢው ስገባ ርዕዮት በፒካፕ መኪና ተጭና እየወጣች ነበር፡፡
የፍርድ ቤቱ የቀጠሮ ሰዓት የተለወጠው ባጋጣሚ ወይም በስህተት ሊሆን ይችላል በሚል ይህ ለምን እንደሆነ መዝገብ ቤቱን ጠይቀን የተረዳነው ኬዙን ያየችው ዳኛ በህመም ምክኒያት ለረጅም ጊዜ ስራ የምትገባው ከሰዓት በኋላ ብቻ መሆኑንና ሁኔታው ለእነሱም እንግዳ ነገር መሆኑን ነው፡፡ ስለዚህም የቀጠሮው ሰዓት ለውጥ በፖሊስ ፍላጎት ሆን ተብሎ ተፈጽሟል ለማለት ይቻላል፡፡ ይህ ማለት በፍርድ ቤቱና በፖሊስ መሀከል ሊኖር የሚገባው መስመር ላይ ችግር አለ ማለት ነው፡፡
ሌላው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለ5 ወራት ያህል ግራና ቀኙን ሲያከራክር ሰንብቶ ታህሳስ 17 2004 ዓ.ም የመጨረሻውን ፍርድ ለመስጠት በተሰየመበት ዕለት የነበረው ሁኔታ እንዲሁ ጥርጣሬውን የሚያጠናክር ነው፡፡ ቀጠሮው ከጠዋቱ 3፡00 የነበረ ቢሆንም በዚያን ዕለት ይሰጣል የተባለውን ፍርድ ለመስማት የተገኙ ሰዎች የችሎቱን አዳራሽ የሞሉት ቀደም ብለው ነበር፡፡ ዳኞቹ 1 ሰዓት አርፍደው 4፡00 ላይ ችሎቱ ተሰየመ፡፡ ወዲያውኑ ውሳኔው ማለቁንና ይሁን እንጂ በኮምፒውተር ተጽፎ ስላላለቀ ከሰዓት በኋላ እናርገው አሉ፡፡ በዚህ ጊዜ የእነውብሸት ጠበቃ አቶ ደርበው “ከሰዓት ሌላ ቀጠሮ ስላለኝ አልችልም” ብለው ከአራት ቀን በኋላ ለታሀሳስ 21 እንዲሆን አማራጭ አቀረቡ፡፡ ዳኛው ግን አልተቀበሉትም፡፡ “እነዚህ ሰወች ያሉት በማረሚያ ቤት ነው፤ ቀጠሮው ከሚራዘም 7 ሰዓት እንገናኝና እስከ 8፡00 እንጨርሳለን” የሚል አማራጭ አቅረቡና በዚሁ ተስማሙ፡፡
የዳኛው ንግግር የሆነ ጥሩ ነገር ሊኖር ይችላል የሚል ተስፋ ስላጫረብን ሁላችንም ከዚያው ሳንወጣ ሰዓቱ እስኪደርስ መንቆራጠጥ ያዝን፡፡
አይደርስ የለ ሰዓቱ ደርሶ ችሎቱ በሚሰየምበት አዳራሽ ተኮለኮልን፡፡ ዳኞቹ ግን በሰዓቱ የሉም፡፡ ግማሽ ሰዓት አለፈ፤ አልመጡም 8 ሰዓት ሲሆን ሁላችንም ቀጠሮ አለኝ ያሉትን ጠበቃ ደርበውን እያየን መሳቀቅ ያዝን፤ ሰዓቱ እየነጎደ ነው፤ 9 ሰዓት ሆነ፡፡ ዳኞቹም አልመጡም ጠበቃ ደርበውም አልሄዱም፡፡ 9፡45 ላይ ዳኞቹ መጡ፡፡ አቶ ደርበው ግን ቀሩ፡፡
ዳኛው ስለማርፈዳቸው ምንም ሳይሉ አሁንም ጽሁፉ ስላልደረሰ በሚል ተለዋጭ ቀጠሮ ለመስጠት አጀንዳቸውን ማገላበጥ ያዙ፡፡ “አራት ቀን ምን ሲደረግ ይራዘማል” ያሉት ዳኛ ከ23 ቀን በኋላ ለጥር 10 2006ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተው ዕለቱና ችሎቱ አበቃ፡፡ ተስፋችንም እንዲሁ፡፡
ይህ ሁኔታ አንዳች ደስ የማይል ነገር እየተከናወነ እንዳለ የሚናገር መሆኑ እንዳለ ሆኖ ቀደም ሲል ያነሳነውን ጥርጣሬ ወደ እውነት የሚገፋው ተጨማሪ ክስተት፣ ለቀጠሮው መራዘም ምክኒያት ሆኖ የቀረበው ነገር ነው፡፡ የታህሳስ 17ቱ ቀጠሮ ወደ ጥር 10 የተሻገረው ውሳኔው በኮምፒውተር ተጽፎ አለማለቁ ሆኖ ሳለ ዳኛው ጥር 10 ያነበቡት በኮምፒውተር ያልተተየበ የእጅ ጽሁፍ ነበር፡፡ ስለዚህም የቀጠሮ ለውጡ የተካሄደው ከችሎቱ ጀርባ ባለ ሌላ ምክኒያት እንጂ ዳኛው እንዳሉት የኮምፒውተር ጽሁፍ ጉዳይ አይደለም ለማለት ይቻላል፡፡
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎችም ትንንሽ የሚመስሉ በርካታ ትዝብቶች ዳኛው የተጻፈለትን እንዳነበበ ከሚገልጸው መረጃ ጋር ተደምረው ሲታዩ የሚሰጡትን ትርጓሜ በማስረጃ ለማረጋገጥ መጠነኛ ጥረቶች ተደርገዋል፡፡
ይህን ለማረጋገጥ ሁነኛና ቀላል ዘዴ ሊሆን የሚችለው በእለቱ ዳኛው ያነበበውን የእጅ ጽሁፍና የዳኛውን ትክክለኛ የእጅ ጽሁፍ አግኝቶ ማመሳሰል ነው፡፡ በዚሁ መሰረት ይህን ለማድረግ የሚያስችሉ ማስረጃዎች ተገኝተዋል፡፡ ማስረጃዎቹ ዳኛው በዕለቱ ያነበበው ጽሁፍ በራሱ በዳኛው የተጻፈ አለመሆኑን የሚያሳዩ ናቸው፡፡
ቀጣዮቹን ሁለት ምስሎች ይመልከቱ
               

Sunday, December 22, 2013

የትግሬ ዘረኛ ቡድን የሚገዛትን ሀገርና ሕዝብ የሚጠላና ሀገሩንም ለማጥፋት 24 ሰዓት የሚሠራ መንግሥት ግን እስከ አሁን በታሪክ አልታየም።

የአማራ ዴ/ኃ/ን ለሱዳን ተላልፎ በተሰጠው መሬት ዙሪያ “ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል” የሚል መግለጫ አወጣ

ጋዜጣዊ መግለጫ 
“ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል”!!
ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) የተሰጠ መግለጫ
ታህሣሥ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.
በዓለም ላይ እስከአሁን የተከሰቱ መንግሥታት (ቅኝ ገዥዎችን ጨምሮ) ጨቋኝ (አምባገነን)፣ በዝበዥ፣ ዘራፊ (በሙስና የተዘፈቀ) … ወዘተ ሊሆኑ ይችላሉ። አሁን ኢትዮጵያን በመግዛት ላይ እንዳለው የትግሬ ዘረኛ ቡድን የሚገዛትን ሀገርና ሕዝብ የሚጠላና ሀገሩንም ለማጥፋት 24 ሰዓት የሚሠራ መንግሥት ግን እስከ አሁን በታሪክ አልታየም። ወደፊትም ከወያኔ በስተቀር የሚገዛትን ሀገር፣ ታሪኳንና ሕዝቧን የሚጠላና ሆን ብሎ ለማጥፋትም ቀን – ተሌት የሚጥር መንግሥት በምድር ላይ ይከሰታል ብለን አናምንም። ይህ የትግሬ ዘረኛ ቡድን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን መጥላቱን የሚያሳይ የድርጊቱን ሥንክሣር መዘርዘር ቢቻልም፣ በአሁኑ ሰዓት የተከሰቱ ሁለት ታላላቅ ብሔራዊ ጉዳዮችን ብቻ እንኳ ብናይ ዘረኛው ቡድን ምን ያህል የሚገዛትን ሀገርና ሕዝቧን አምርሮ እንደሚጠላ ፍንትው አድርገው ያሳያሉ፦
  1. በሣዑዲ አረቢያ የወገኖቻችን ደም  በግፍ ሲፈስስ፣ እህቶቻችን ያለርህራሄ በቡድን ሲደፈሩ፣ በ21ኛው ክ/ዘመን በሰው ልጅ ላይ የፈፀማል ተብሎ የማይታሰብ ኢሰብአዊ ግፍ ሲፈፀምባቸውና በአጠቃላይ በሀገሪቱ ላይ ብሔራዊ ውርደት ሲደርስ የትግሬው ዘረኛ ቡድን “የሣዑዲ አረቢያ መንግሥት በሀገሩ ላይ ይህንን ማድረግ መብቱ ነው” ነበር ያለው።
  2. በዚህ ሰቅጣጭ ሐዘን ውስጥ ተውጠንና በስቃይ ላይ ያሉ ወገኖቻችንን ለመርዳት ላይ ታች በምንልበት ጊዜ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ታጥቆ የተነሳው የትግሬው ዘረኛ ቡድን አባቶቻችን ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ ጠብቀው ያቆዩትን 1600 ኪ/ሜ ርዝመትና ከ20-60 ኪ/ሜ ወደ ኢትዮጵያ ጥልቆ የሚገባውን ከሱዳን የሚያዋስነውን ድንበራችንን በሕገወጥነት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ፈርሞ ለሱዳን አስረከበ። ምንም እንኳን በሚስጥር ሊይዘው ቢሞክርም የድንምበር ማካለሉ ከጥር ወር 2006 እስከ መስከረም 2007 ችካል በመቸከል እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።
የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) ይህንን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ የሚደረግ ሕገወጥ የድንበር ክለላ አጥብቆ መቃወምና ማውገዝ ብቻ ሳይሆን እንዳባቶቹ ደሙን አፍስሶና አጥንቱን ከስክሶ ታሪካዊ ድንበሩን ለማስከበር ቆርጦ ተነስቷል። ባንዳ የባንዳ ልጆች ከአባቶቻቸው የወረሱትን ሀገር የማጥፋትና የመሸጥ ውርስ ተግባራዊ ሲያደርጉ እኛ የአርበኛ ልጆች ነን የመንል ይህንን ደባ ዝም ብለን ብንመለከት ድንበር ላይ የተከሰከሰው የአባቶቻችን አጥንት እሾህ ሆኖ ይዎጋናል። በመሆኑም በአካባቢው ያላችሁ ታጋይ ኃይሎችና የገፈቱ ቀማሽ የሆንከው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በርስቱና በሚስቱ ያልሞተ ወንድ ልጅ ወንድ አይደለምና ወንድ ልጅ ነኝ ያልክ ሁሉ ተባበረን፣ ከዚህ በላይ የሞት ሞት የለምና።

አዴኃን ይህንን ድርጊት አምርሮ የሚቃወመው እንዲያው በጭፍኑ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር ሕጋዊ የሆነ ድንበር አይኑራት ብሎ አይደለም። የድንበር ስምምነቱ ኢትዮጵያን ጎድቶ ሱዳንን የሚጠቅም፣ ከ110 ዓመታት በፊት የፈረሰና ሕጋዊ ያልሆነ ውልን መሠረት ያደረገ፣ በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ጥናት ያደረጉ ኢትዮጵያውያንን ጥናትና ውትወታ ግንዛቤ ውስጥ ያላስገባና በአጠቃላይ ከኢትዮጵያ  ሕዝብ ጀርባ በደባና በሕገወጥነት የተፈረመ ውል በመሆኑ እንጅ።

በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ጥናት ያደረገው የኢትዮጵያ የድንበር ኮሚቴና ከዚያ በፊትም ጥናት ያደረጉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምሑራን እንደሚሉን ከሆነ ይህ ዛሬ የትግሬው ዘረኛ ቡድን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ለተፈራረመው ውል ዋቢ የሚያደርገው ውል በዳግማዊ አፄ ምኒልክና በጊዜው የሱዳን ቅኝ ገዥ በነበረችው እንግሊዝ መካከል የተፈረመው እ.አ.አ 1902 ነበር። አፄ ምኒልክ ይህንን ውል የፈረሙት በኃይል ተገድደውና በይዞታቸው ሥር የነበሩ ብዙ መሬቶችን ለቀው ነበር። በዓመቱ በ1903 የእንግሊዙ የጦር መኮንን ሻለቃ ጉዊን ድንበሩን ከስምምነቱ ውጭ ብቻውን ሄዶ ከመከለሉም በላይ አፄ ምኒልክ ተገድደውም ቢሆን የፈረሙትን ካርታ አዛብቶ ኢትዮጵያን እየጎዳ ችካል ቸከለ።
ይህንንም ሻለቃ ጉዊን ከተሰጠው ሥልጣን በላይ ሄዶ መሥመሩን በማዛባት ከኢትዮጵያ መሬት እንደወሰደ በራሱ ሪፖረት ላይ በግልፅ ሳይደብቅ ጽፏል። እንግሊዞችም በ1902 የተፈረመበትን ካርታ ጥለው በችካሉ መሠረት በ1903 አዲስ ካርታ በመሥራት እነርሱ ከፈረሙበት በኋላ አፄ ምኒልክን ለማስፈረም ቢሞክሩም ከስምምነት ውጭ ለተቸከለው የጉዊን ክለላ ዕውቅና በመንፈግ ሳይፈርሙበት ቀርተዋል። የትግሬው ዘረኛ ቡድን አፄ ምኒልክ፣ አፄ ኃይለሥላሴና ደርግ የጉዊንን መሥመር ተቀብለዋል እያለ የሚያላዝነው ይህንን የመሰለውን ሐቅ በመካድ ነው። ይህንንም ዓይን ያወጣ የወያኔን ቅጥፈት አዴኃን ብቻ ሳይሆን ሰኞ 19 ኖቬምበር 2007 (እ.አ.አ.) ሱዳን ትሪቢዩን የተባለ ጋዜጣም “ድንበሩን አስመልክቶ የሱዳን መንግሥት ከቀደምት የኢትዮጵያ መንግሥታት ጋር የነበረው ግንኙነት ቀና አልነበረም። በድንበሩ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር የመጀመሪያው ፈቃደኛ መንግሥት ገዥው የኢሕአዴግ መንግሥት ብቻ ነው” በማለት መሥክሮበታል።
ጥሪ፦     
ውድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራትም ጭምር፣ ይህ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ በሀገር ከሃዲው የትግሬ ዘረኛ ቡድ ከጎንደር፣ ከጎጃም፣ ከወለጋና ከኢሊባቡር ክፍለ ሀገሮች ተቆርሶ ለሱዳን የሚሰጠው ለም መሬት የክፍለ ሀገራት ተወላጆቹ መሬት ብቻ አይደለም፤ የአንተም የኢትዮጵያዊው መሬት እንጅ። በመሆኑም አዴኃን ይህንን በባንዳ ልጆች የተጋረጥብንን ኢትዮጵያን የማጥፋት ታላቅ አደጋ ለመቀልበስ ስንል ያሉንን ጥቃቅን ልዩነቶች ወደጎን በመተው፣ ከምንጊዜውም በላይ እጅ ለእጅ ተያይዘንና ያለንን አቅም ሁሉ አስተባብረን በመነሳት የዜግነት ግዴታችን እንድንወጣ አስቸኳይ ጥሪውን ያስተላልፋል። “ዳሩ ክልተጠበቀ፣ መሀሉ ዳር ይሆናል” እንደሚባለው የትግሬውን ዘረኛ ቡድን በተባበረ ክንድ ዛሬውኑ ካላስወገድነው በስተቀር እናት ሀገራችን ኢትዮጵያን የማፈራረስ ዕኩይ ተልዕኮው የድንበር መሬቶችን እየቆረሰ ለጎረቤት ሀገራት በመስጠት ብቻ ያቆማል ብሎ ማሰብ ፍፁም የዋህነት ነው።

ለመከላከያ ሠራዊት፣ የፖሊስ ኃይልና የኢሕአዴግ ደጋፊዎች፣ እናንተ የምትደግፉት ሀገር አጥፊው የትግሬ ዘረኛ ቡድን አባቶቻችን ደረታቸውን ለጦር፣ እግራቸውን ለጠጠር ሰጥተው በደማቸው ያቆዩአትን ይህችን ጥንታዊትና ታሪካዊት ሀገራችንን እያጠፋት እንደሆነ ለእናነተ የተሠወረ አይደለም። ይህንን ሀገር የማጥፋት ወንጀል የሚፈፅመው ደግሞ እናንተን በመሣሪያነት በመጠቀም ስለሆነ ይህንን ተገንዝባችሁ አሁኑኑ ከሕዝባችንና አደጋውን ለመቀልበስ ከሚታገሉ ኃይሎች ጎን በመቆም ሀገራችሁን እንድትታደጉ ስናሳስብ፣ ጥሪያችን ችላ በማለት ለሀገር አጥፊው ቡድን ተባባሪነታችሁን ከቀጠላችሁበት ግን ታሪክና ሕዝብ ይቅር እንደማይላችሁ በጥብቅ ልናስጠነቅቃችሁ እንወዳለን።

ለብአዴን አባላት፦ “እሣት አመድ ይወልዳል” እንደተባለው ካልሆነ በስተቀር፣ አባቶቻችሁ ኢትዮጵያን ከሚያጠፋ ጠላት ጋር ተባብረው እናት ሀገራቸውን አላጠፉም፤ ይልቁንም ደማቸውን አፍስሰውና አጥንታቸውን ከስክሰው የታፈረችና አንድነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለእናንተ አስረከቧችሁ እንጅ። እናንተ ግን የጀግኖች አባቶቻችሁ የባሕሪ ልጆች መሆን አቅቷችሁና አደራቸውን በልታችሁ ኢትዮጵያን ለማፈራረስና አማራን ለማጥፋት ቆርጦ ለተነሳው የትግሬ ዘረኛ ቡድን አሽከር ሆናችሁ እናት ሀገራችሁንና ወገናችሁን እያጠፋችሁ ነው። “ለእንጀራየ፣ ለልጆቼና ለቤተሰቦቼ ስል ወይም ተገድጀ ነው ይህንን የማደርገው” የሚለው ውሃ የማይቋጥር ምክንያት እንደማያዋጣችሁ አውቃችሁ የጋራ ሀገራችንንና ወገናችንን ለመታደግ አብራችሁት እንደትቆሙ አዴኃን ከልብ የመነጨ የሀገር አድን ጥሪ ያቀርብላችኋል።

ወንድም ለሆነው የሱዳን ሕዝብ፦ የኢትዮጵያና የሱዳን ሕዝብ ለብዙ ሺህ ዘመናት ከአንድ ወንዝ ከተቀዳ ውሃ እየጠጣ፣ በመከባበር ላይ በተመሠረተና በመልካም ጉርብትና አንዱ ለሌላው የችግር ጊዜ ደራሽ ሆኖ የኖረ ወንድማማች ሕዝብ ነው። ነገር ግን ዛሬ የትግሬው ዘረኛ ቡድን በሀገር ውስጥ የሚገኙ ነገዶችን እርስ በእርሳቸው ከማናከስ አልፎ የኢትዮጵያን ሕዝብ በተለይም የአማራውን ነገድ ወንድም ከሆነው የሱዳን ሕዝብም ለማናከስ ቆርጦ የተነሳ በመሆኑ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ዕውቅና ውጭ የተፈረመን የድንበር ስምምነት እንዳይቀበል በጥብቅ እናሳስባለን።

በመጨረሻም የዓለም ምንግሥታትና ዓለም – አቀፍ ሠላም ወዳድ ሕብረተሰብም የወያኔ ዘረኛ ቡድን ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ሕዝብ ፈፅሞ እንደማይወክልና አሁን ከሱዳን መንግሥት ጋር በድብቅ የተፈራረመውንም የድንበር ስምምነት ንቅናቄያችን አዴኃን እና የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደማያውቁት ተገንዝበው ስምምነቱ አሁንም ይሁን ወደፊት በሁለቱ ሀገራት ሕዝብ መካከል የሚፈጠረውን ቀውስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ለስምምነቱ ዕውቅና እንዳይሰጡና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚፈፀመውን ይህንን ሤራ እንዲቃወሙ አዴኃን ጥሪውን ያስተላልፋል።
በደም የተረከብናትን ሀገር በደም እንጠብቃታለን!!

Saturday, December 21, 2013

በኩላሊት ህመም የሚሰቃየው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በቂ ህክምና ሳያገኝ ወደ ዝዋይ እንዲመለስ ተወሰነ

ዘጋቢ ጋዜጠኛ ዳዊት ሰለሞን ከአዲስ አበባ

በዝዋይ ወህኒ ቤት ቆይታው ለከፍተኛ የኩላሊት ህመም በመዳረጉ የተሻለ ህክምና ያገኝ ዘንድ በማረሚያ ቤቱ ክሊኒክ ሪፈር የተጻፈለት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ወደ አዲስ አበባ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ቢዘዋወርም የናፈቀውን የተሻለ ህክምና ሳያገኝ ወደ ዝዋይ ማረሚያ ቤት እንዲመለስ መወሰኑን ለጉዳዮ ቅርበት ያላቸው ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

ውብሸት ከቤተሰቦቹ ራቅ ባለ የዝዋይ ማረሚያ ቤት የእስር ጊዜውን እንዲገፋ በመደረጉ በየጊዜው መጎብኘት የተሳናቸው ቤተሰቦቹ በቅርበት ሊጎበኙት ወደሚችሉበት ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወር ሲጠይቁ መቆየታቸው አይዘነጋም፡፡የቀድሞው የአውራምባ ታይምስ ምክትል አዘጋጅ ወደ ቃሊቲ እንዲዘዋወር ከተደረገ በኋላም ጤንነቱ ምንም አይነት መሻሻል ባለማሳየቱ ህክምና የማግኘት መብቱ እንዲከበርለት የማረሚያ ቤቱን ሃላፊዎች ሲጠይቅ ቆይቷል፡፡

ጋዜጠኛው ህክምና ለማግኘት በሚጠባበቅበት ሰዓት ወደ ዝዋይ እንዲመለስ መወሰኑ በቤተሰቦቹ ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ ፈጥሯል፡፡ከዚሁ ጋር በተያያዘ አበበ ቀስቶና አቶ በቀለ ገርባ በተመሳሳይ መልኩ ከዝዋይ ማረሚያ ቤት ህክምና ማግኘት ወደሚችሉበት ቃሊቲ እንዲዘዋወሩ ቢደረግም ህክምና የማግኘት መብታቸውን የቃሊቲ አመራሮች ባለማክበራቸው ከእነህመማቸው እንደሚገኙ ምንጮቼ ጠቁመዋል፡፡

Thursday, December 19, 2013

የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን በማሰጠትና ለዜጎች ሞት የሚጠየቁት አቶ አያሌው ጎበዜ ስልጣናቸውን ለቀቁ


(ዘ-ሐበሻ) የአማራ ክልል መሬቶች ለሱዳን እንዲሰጡ ከገዢው ሕወሓት ጋር በመተባበር ወንጀል፣ እንዲሁም ከጉራፈርዳ ተባረው ወደ አማራ ክልል የመጡ ዜጎች የሚቀበላቸው የክልል መስተዳድር ጠፍቶ ለርሃብና ለሞት በመዳረጋቸው በዚህም ወንጀል እንደሚጠየቁ የሚነገርላቸው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አያሌው ጎበዜ ስልጣናቸውን አስረከቡ።
አቶ አያሌው ጎበዜ
መንግስታዊ ሚድያዎች አቶ አያሌው ጎበዜ “በመተካካት” ሂሳብ ስልጣኔን ተረክበውኛል ሲሉ ይዘግቡ እንጂ የአማራ ክልል ምክር ቤት 
በአስቸኳይ ተሰብስቦ ይሄን ውሳኔ ማጽደቁ            አቶ ገዱ አንዳርጋቸው
ከበስተጀርባው የተደበቀ ምስጢር ሳይኖር እንዳልቀረ ብዙዎች ይገምታሉ። በተለይም አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ሰሞኑን አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ከሱዳን ጋር የኢትዮጵያን መሬቶች አሳልፈው ለመስጠት ከተፈራረሙ በኋላ የአቶ
አያሌው ስልጣኔን ልልቀቅ ጥያቄ ምንልባትም ለሱዳን ከሚሰጠው የኢትዮጵያ መሬት ጋር በተያያዘ ሊሆን እንደሚችል አስተያየታቸውን ለዘ-ሐበሻ ሰጥተዋል።
የአማራ ክልል አስቸኳይ ስብሰባውን ከትናንት ምሽት ጀምሮ በባህር ዳር ያካሄደው የአማራ ክልል ምክር ቤት ክልሉን ላለፉት 8 ዓመት ተኩል የመሩትን የአቶ አያሌው ጎበዜን ጥያቄ ወዲያውኑ በመቀበል ከስልጣን ያወረዳቸው ሲሆን በምትካቸውም በሕወሓት ተላላኪነታቸው ከአቶ ደመቀ መኮንን አይተናነሱም የሚባሉት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ተተክተው ተሾመዋል። አቶ ገዱ የአማራ ክልል ም/ል ፕሬዚዳንትና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን አቶ አያሌው አልፈጽምም ሲሉ የነበሩ ሥራዎችን ለሕወሓት በማደር ይሰሩ እንደነበር እርሳቸውን የሚያውቁ ወገኖች ለዘ-ሐበሻ ጠቁመዋል። በተለይም አምባገነንና እኔ ያልኩት ይድመጥ የሚል ባህሪይ እንዳላቸው የሚነገርላቸው አቶ ገዱ የአማራ ክልል ስር ያሉ የኢትዮጵያ መሬቶችን ለሱዳን በመስጠት ከሕወሓት ጋር አብረው እንደሚሰሩ ይጠበቃል።
አቤል የተባሉ በክልሉ የሚኖሩ በፌስቡክ ዘ-ሐበሻን የሚከታተሉ አንድ አስተያየት ሰጪ በሰጡት አስተያየት “ክልል ርዕሰ መስተዳድር የነበሩት ክቡር አቶ አያሌው ጎበዜ ዛሬ በአቶ ደጉ አንዳርጋቸው የተተኩበት አስቸኳይ ጉባኤ አንደምታው ምን ይሆን? ምን አልባት ከሠሞኑ የሚሠሙ ወሬዎችን እልባት ለመስጠት ይሆን? ያ ማለt ዐድርቃይን ለትግራይ፣ መተማን ለሱዳን፣ ጃዊ አካባቢ ያለ የአማራ ክልል ግዛቶችን ለመስጠት መሠናክሉን ከወዲሁ ለማቅለል ይሆን እንዴ? ያ ምርጫ፣  ዘመን ሣይጠናቀቅ ከስልጣን አቶ አያሌውን ማንሣት ምን ማለት ነው? እርሣቸው ለክልሉ ልዑላዊነት መከበር ጥብቅና የሚቆሙ ታማኝ መሪ ስለነበሩ ገለል ለማድረግ የታለመ ሹም ሽር ነው የሚል ግምት አለኝ” ብለዋል።
ሌላው የዘሐበሻ የፌስቡክ ተከታይም እንዲሁ “የአማራን ክልል መሬት ለሌላ አሳልፌ አልሰጥም በማለታቸው ስልጣናቸውን እንደለቀቁ ነው” የማምነው ሲሉ አስተያታቸውን ሰጥተውናል።
አንድ ቀን በኢትዮጵያ ነፃነት ሲመጣ ምንም እንኳ እርሳቸው አልፈረሙም፤ የፈረሙት አቶ ደመቀ መኮንን ናቸው የሚባል ወሬ ቢኖርም አቶ አያሌው ጎበዜ ለሱዳን በተሰጠው መሬት፣ በአማራ ክልል ለደረሱ ጭፍጨፋዎች፣ በዜጎች መፈናቀል ዙሪያ ላሳዩት ቸልተኝነት ለፍርድ ይቀርባሉ የሚሉ ወገኖች ብዙ ናቸው።

Wednesday, December 18, 2013

ኦባንግ ከደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ጋር ተነጋገሩ

“በራችሁን ዘግታችሁ እርቅ አውርዱ”

* “ባለውለታችሁ የኢትዮጵያ ህዝብ አዝኖባችኋል፣ አርቃችሁ እዩ”
“በትግሉ ወቅት ለነጻነት ስትዋደቁ ኢትዮጵያ በጋምቤላ አኙዋክ ምድር ላይ ሙሉ ከለላና ዋስትና በመስጠት ያበረከተችው አስተዋጽኦ የሚረሳ ነው? ከነጻነት ታጋዮችችሁ ጎን በመሰለፍ ብረት ያነሱ የአኙዋክ ኢትዮጵያውያን ልጆች መስዋዕትነት ይዘነጋችኋል? አሁን ድረስ የትግሉ የመስዋዕትነት ቁስላቸው ያልዳነ የአኙዋክ ልጆች እንዳሉ ትዘነጋላችሁ?” በማለት የተናገሩት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ /ጥቁሩ ሰው/ ናቸው።
በታላላቅ መድረኮችና በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ተሰሚነታቸውና ስብዕናቸው እየጎላ የሄደው ጥቁሩ ሰው ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ ከላይ የተገለጸውን ህሊና የሚፈታተን ጥያቄ ያቀረቡት ለደቡብ ሱዳን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ባርናባ ማሪያል ቤንጃሚን ነው። ለረዥም ሰዓት ጊዜ ወስደው ውይይት ማድረጋቸውን ተከትሎ የጎልጉል የአሜሪካ ዘጋቢ እንደዘገበው አቶ ኦባንግ ዶ/ር ባርናባን ያገኟቸው አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ነበር።
በጁባ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መደረጉ ይፋ ከተደረገበት አንድ ቀን በፊት አስቀድሞ በተያዘ የውይይት መርሃ ግብር የተገናኙት ዶ/ር ባርናባና አቶ ኦባንግ በርካታ ወቅታዊ ጉዳዮችን አንስተው መነጋገራቸው ታውቋል። አቶ ኦባንግ የደቡብ ሱዳን የነጻነት ትግል ወቅት ኢትዮጵያ በመንግስት ደረጃ የሰጠችውን ሙሉ ድጋፍና፣ ድንበር ሳይከልላቸው በሁለቱም አገራት የሚገኙት የአኙዋክ ልጆች ትግሉን የነፍስ ዋጋ በመክፈል መደገፋቸውን በማስታወስ በውይይቱ ወቅት ያነሱት ያለ ምክንያት አልነበረም።
“በጆን ጋራንግ ይመራ የነበረው ትግል ፍሬ አፍርቶ ደቡብ ሱዳን ነጻ ስትወጣ የማይረሳ ውለታ ለሰራቸው ኢትዮጵያና የአኙዋክ ልጆች የተከፈላቸው ብድር አሳዛኝና የወደፊቱን ጊዜ ያላገናዘበ ነው” በማለት በውይይቱ ስለተነሱ ነጥቦች ማብራሪያ የሰጡት አቶ ኦባንግ፣ “ለህዝቦች ነጻነትና ለሰብአዊ መብት መከበር የታገለ ድርጅትና አመራሮች ለነጻነታቸው የተከፈለላቸውን የደም ዕዳ ያወራረዱትና እያወራረዱ ያሉት ከወያኔ መሪዎች ጋር በማበር ከለላ የጠየቁ ህጋዊ ስደተኞችን እያፈኑ ለወያኔ አሳልፎ በመስጠት መሆኑ አሳዝኖኛል። ኢትዮጵያዊያን አዝነዋል” በማለት ነበር።
ህጋዊ ከለላ የጠየቁ ስደተኞች ቶርቸር እንዲደረጉ፣ እንዲገደሉ፣ እንዲታሰሩና ኢሰብአዊ ግፍ እንዲፈጸምባቸው ለአምባገነኖች አሳልፎ መስጠት ዘግይቶም ቢሆን ዋጋ እንደሚያስከፍል አቶ ኦባንግ አስረግጠው ተናግረዋል። በ1993 የአኙዋክ ጄኖሳይድ /የጅምላ ጭፍጨፋ/ ሸሽተው በስደት ደቡብ ሱዳን የገቡ የአኙዋክ ልጆችን ለገዳዩ የወያኔ አንጋች ሃይል ማስረከብ መቆም እንዳለበት ያሳሰቡት አቶ ኦባንግ “ይህንን ተግባር የፈጸሙትም ቢያንስ ዓለም አቀፋዊውን ህግ ተላልፈዋልና ሊጠየቁ ይገባል። እርስዎም ይህንኑ የማስፈጸም ሃላፊነት ይኖርብዎታል” በማለት ለውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
የአኙዋክና የበኩር ልጆችና የደቡብ ሱዳን ግንኙነት ከድንበር ያለፈ የደም ትስስርና ኢትዮጵያ የማይረሳ ውለታ በመክፈል ያከበረችው ውህደት በመሆኑ መንግስታቸው ቆም ብሎ ሊያስብ እንደሚገባው አቶ ኦባንግ ምክር አዘል መልዕክት ማስተላለፋቸውን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ አስተማማኝ ከለላና ዋስትና በመስጠት የፈጸመችውን ሊዘነጋ የማይችል ተግባር አለማክበር ለወደፊቱ ወዳጅ የሚያሳጣ ብድር ለራስ የማስቀመጥ ያህል እንደሆነም በወጉ እንዲገነዘቡ ሚኒስትሩን ተማጽነዋል።
photoአምባገነኑና በህዝብ የሚጠላው የህወሃት አገዛዝ እድሜ አሁን ካለው ትውልድ እድሜ በላይ ዘሎ የሚሄድ ባለመሆኑ በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ የፖለቲካ ድርጅቶችን ማቅረብ፣ መተዋወቅና መልካም ግንኙነት መመስረት ለወደፊቱ ጠቃሚ መሆኑንም አስረድተዋል። እርሳቸው በዋና ዳይሬክተርነት የሚመሩት ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄም /አኢጋን/ ከተመሰረተበት ዓላማ አንጻር የደቡብ ሱዳን መንግሥት ህወሃት/ኢህአዴግን ለማስደሰት ሲል ኢትዮጵያዊያን ላይ ፈጸመውና እየፈጸመ ባለው ተግባር ያዘኑ ወገኖች የቀድሞውን የፍቅር መንገድ እንዲከተሉ አበክሮ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ሕዝብ ያልወደደው መንግስትና ህዝብ ያልተቀበለው ኢንቨስትመንት መጨረሻው ኪሳራ በመሆኑ የደቡብ ሱዳን መንግስት ሊጠነቀቅ እንደሚገባው አቶ ኦባንግ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ነግረዋቸዋል። ከደቡብ ሱዳን ተነስቶ በጋምቤላ አድርጎ ወደ ኬኒያና ጅቡቲ ይዘረጋል የተባለው የነዳጅ ማስተላለፊያ ቱቦ ሕዝብን በመግፋትና በመበደል ከቶውንም ተግባራዊ ሊሆን እንደማይችል ያለማቅማማት ጠቁመዋል።
ህዋሀት በጋምቤላ ንጹሃንን ከቀያቸው በጠመንጃ ሃይል በማባረር፣ መሬታቸውን በሳንቲም ቸብችቦ፣ የህይወታቸው ዋስትና የሆነውን ደናቸውን አስጨፍጭፎ፣ ለምን በማለት የጠየቁትን አስሮና ገድሎ ያቋቋመው ኢንቨስትመንት በዜሮ መጣፋቱን ለአብነት ጠቅሰው ማስረዳታቸው የጠቆሙት ጥቁሩ ሰው “ኢንቨስትመንት መልካም ነው። ህዝብ ካልተቀበለው ተግባራዊ ሊሆን አይችልም። ህዝብ ይሁንታ የማይሰጠው ኢንቨስትመንት ፍሬ አያፈራም። ከውስጥም ከውጪም ያላችሁን ግንኙነት መርምሩ። ያዘኑባችሁ ተበራክተዋል” ሲሉ መክረዋል።
በአዲስ የምትቋቋመው “አዲሲቷ ኢትዮጵያ” ለደቡብ ሱዳን ወንድምና እህቶች ጭምር ቦታ በማዘጋጀት መሆኑንን አቶ ኦባንግ አረጋግጠው “በሌላ በኩል ደግሞ በአሁኑ ወቅት ስጋት ውስጥ መሆናቸውን ተናግረዋል። ለዲሞክራሲ መከበርና ለነጻነት በተከፈለው መስዋዕት የተገኘውን ድል የደቡብ ሱዳን መንግስት በአግባቡ እየተጠቀመበት አለመሆኑን አቶ ኦባንግ ለውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገልጸውላቸዋል። አዲሲቷ ደቡብ ሱዳን ከድል በኋላ የትግሉን መሐላ ሙሉ በሙሉ ረግጣለች በማለት መሪዎቹን ወቅሰዋል።
ከድል በኋላ በደቡብ ሱዳን በርካታ ችግሮች መከሰታቸውን በመዘርዘር የማስጠንቀቂያ ምክር መሰንዘራቸውን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “አሁን ባለው ሁኔታ በደቡብ ሱዳን ባሉ ሃያ አንድ ጎሳዎች መካከል ቀውስ መፈጠሩ አይቀርም። ስለዚህ በራችሁን ዘግታችሁ እርቅ አውርዱ። በቀደሙት ሰማዐታቶች ደምና አጥንት ላይ ዴሞክራሲን መስርቱ። ይህንን ካላደረጋችሁና አሁን በያዛችሁት የአምባገነንነትና የአንድ ሰው ወይም ጎሣ የበላይነት መንገድ ከቀጠላችሁ ጣጣው ወደኛም ያመራል” ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን አስጠንቅቀዋቸዋል። አሁን ያለው የውስጥ ሽኩቻ መልኩን ሳይቀይር መፍጠን እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋቸዋል። (አቶ ኦባንግ ይህንን ለውጭ ጉዳይ ሚ/ሩ የተናገሩት እሁድ መፈንቅለ መንግሥት ከመሞከሩና አሁን ደግሞ በዘር /ጎሣ/ መስመር ተከፋፍለው ደቡብ ሱዳናውያን መጫረስ ከመጀመራቸው አንድ ቀን በፊት ነበር)
ambassador 1
አቶ ኦባንግ በአሜሪካ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ጋር
በደቡብ ሱዳን እውነተኛ እርቅ ለማውረድ የአኙዋክ የፍትሕ ምክርቤት አንድ ግብረ ሃይል ወደ ጁባ እንደሚልክ መረጃ እንዳላቸው የጠቆሙት አቶ ኦባንግ በውይይቱ ወቅት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቀና ምላሽ ማግኘታቸውን አመልክተዋል። በመጨረሻም አቶ ኦባንግ የሚመሩት ድርጅት ኢትዮጵያ ውስጥ የእርቅ ደጆች የሚከፈቱበት አግባብ ላይ ከሚመለከታቸው ተጽዕኖ አድጊራዎችና አቅሙ ካላቸው አካላት ጋር እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸውላቸዋል። በማያያዝም “እኛ ሩቅ እያየን እየሰራን ነው። እኛ በስፋት እያሰብን በመራመድ ላይ ነን። በስፋት አስበን፣ ሩቅ እያየን ስንሰራ እናንተንም አንዘነጋም። በተቃራኒው እናንተ ለነጻነታችሁ የተዋደቁላችሁን የራሳችሁን ዜጎች እያነቃችሁ ለወያኔ አሳልፋችሁ ትሰጣላችሁ። ደም ያፈሰሱላችሁንና አጥንታቸውን የከሰከሱላችሁን ውድ ዜጎች ሳትታረቁ በምድራቸው ላይ ቱቦ ዘርግታችሁ ብር ልታመርቱ ታቅዳላችሁ። ይህ ከቶውንም ጤነኛ አካሄድ አይደለምና ህዝብን አስቀድሙ። አብረን እንስራ። ይህ መልካም ጅምር ነው” በማለት መሰናበታቸውን አቶ ኦባንግ ለጎልጉል ተናግረዋል።
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክትር አቶ ኦባንግ ሜቶ ከደቡብ ሱዳን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ባርናባ ማሪያል ጋር ለመወያየት የቻሉት ሚኒስትሩ አሜሪካ ከመምጣታቸው በፊት በኤምባሲያቸው አማካይነት አስቀድሞ በተያዘ መርሃ ግብር መሰረት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። በውይይቱ ወቅት ሚኒስትሩ ስለ ሰጡት አስተያየትና ምላሽ አቶ ኦባንግ በዝርዝር ለመናገር አልፈለጉም። አቶ ኦባንግ በትውልድ አኙዋክ ቢሆኑም እርሳቸው የሚመሩት ድርጅት /አኢጋን/ ኢትዮጵያውያን ከአገራቸው ውጭ በስደት በሚሰቃዩበት ቦታ ዘር፣ ቀለም፣ ጎሣ፣ ቋንቋ፣ ወዘተ ሳይለይ ፈጥኖ በመድረስ እርዳታ በማድረግ እርሳቸውም በተመሳሳይ ተግባር ተጠምደው በቅንነት በማገልገል እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የእርቅ ደጆች እንዲከፈቱ አግባብ ካላቸውና አቅሙ ካላቸው ክፍሎች ጋር እየሰራን ነው በማለት አቶ ኦባንግ ለሚኒስትሩ የገለጹላቸውን ሃሳብ እንዲያብራሩ ከጎልጉል ተጠይቀው “ሁሌም የእርቅ ደጆች እንዲከፈቱ እንሰራለን። ይህ የጋራ ንቅናቄውና አርቀው የሚመለከቱ ዜጎች ሁሉ እምነት ነው። ብዙ ስራ እየሰራን ነው። ስንጨብጠውና ለህዝብ ሪፖርት የምናቀርብበት አሳማኝ ጊዜ ላይ ስንደርስ ብቻ ይፋ እናደርጋለን። ስራው በባህሪው ከንግግር በመቆጠብ ተግባር ላይ ማተኮርን ስለሚጠይቅ እኛም ባናወራው ጊዜው ሲደርስ ሁሉም በየፊናው የሚገልጸው ይሆናል። ስራው ሳይሰራ ፕሮፓጋንዳው ከቀደመ በሁሉም ወገን ተዓማኒነትን የማጣትና የመጣል አደጋ አለው። የኢትዮጵያ ህዝብ ተግባር የናፈቀው ይመስለኛል” የሚል ድፍን መልስ ሰጥተዋል።(http://www.goolgule.com/)

Tuesday, December 17, 2013

የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል የተመሰረተበትን አንደኛ አመት አስመልክቶ የተሰጠ ድርጅታዊ መግለጫ

December 17, 2013

ታህሳስ 7  2006 ዓም የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ከተመሰረተ  አንድ አመት ሞላው። አንድ አመት  በጭንቅና  በአሳር  ለተያዘች የዛሬይቱ ኢትዮጵያና ህዝቧ እጅግ ረጅም ግዜ እንደሆነ ህዝባዊ ሃይሉ በሚገባ  ይገነዘባል። ባላፈው አንድ አመት ውስጥ የኢትዮጵያን ህዝብ የመከራ የአሳርና የውርደት ህይወት ይበልጥ እየሰፋ፣ የሚፈጸምበት ግፍ ይበልጥ እየገዘፈ መሄዱን አይተነዋል። በሃገርና በህዝብ ላይ እየወረደ ያለውን ወያኔ ወለድ የስቃይና የፍዳ ናዳ በቅጡ ላጤነው  ሃገሪቱና ህዝቧ የአዳዲስ የስቆቃና የመከራ አይነቶች መፈተኛ ቤተ ሙከራዎች እየተደረጉ ለመሆኑ ጥርጥር አይኖረውም። ለሚራበው ለሚረገጠው በግፍ ለታጎረው፣ በኑሮ ውድነት ለሚጠበሰው፣ ለተሰደደው ለተፈናቀለው ኢትዮጵያዊ እንድ አመት በሲኦል የቀናትና የወራት መቁጠሪያ እንደሚለካ ዘመን እጅግ የረዘመ የስቃይ ግዜ ነው።Ginbot 7 Popular Force logo
የዋልድባ መነኩሳት ገዳማችን  አትድፈሩ አታፍረሱ በማለታቸው እየተገረፉ ለዘመናት ፈጣሪያቸውን ከሚማጸኑበት ለሃገርና  ለህዝብ ምልጃ ከቆሙበት ገዳም በዘር መመዘኛ እየተለዩ  እንደቆ ሻሻ ተጠርገው የተባረሩበት ፣ እምነታችን አትንኩ ያሉ የእስልምና እምነት ተከታዮችና  መሪዎቻቸው በሃሰት ክስ ተመስርቶባቸው  ወህኒ መውረዳቸው አንሶ  ወንድሞቻችን ይፈቱ በማለት  ሰላማዊ  ጥያቄ ያቀረቡ ወገኖቻቸን በወያኔ ነፍሰ- ገዳዮች  በአረመኔያዊ ጭካኔ የተጨፈጨፉት በዚሁ አመት ነው። ወያኔ በህዝብ መሃከል በዘራው የዘር መርዝ የተነሳ በሽዎች የሚቆጠሩ አማሮች ከጉራ ፈርዳና ከቤንሻንጉል፣ ኦሮሞዎች ለዘመናት ከኖሩበት ምስራቅ ሃረርጌ  አካባቢ  እንዲፈናቀሉና በገዛ ሃገራቸው መድረሻ ቢሶች  እንዲሆኑ የተደረገው በዚህ አንድ አመት ውስጥ ነው። ጋምቤላዎች ሙርሲዎች አፋሮችና ሌሎችም ብሄረሰቦችና ማህበረሰቦች የተጨፈጨፉበት፣በልማት ስም ለመጡ የውጭ ወራሪዎችና ወያኔ ለፈጠራቸው ቱጃሮች ቦታ እንዲለቁ ተደርጎ ቀደምቶቻቸው ለዘመናት ከኖሩባቸው ቀየዎች እንዲነቀሉ ተደርገው እንደ አልባሌ ነገር የትም እንዲበተኑ የማድረጉ ሂደት ከመቼውም በላይ ተጠናክሮ የቀጠለው በዚሁ አመት ነው። በዚሁ አንድ አመት በወያኔ የሃገሪቱ ገዥዎች በህዝብ ላይ የተፈጸመው  ጭካኔና ወንጀል ተዘርዝሮ  የሚያልቅ አይደለም።
ይህ ወያኔ  ሰራሽ ሃገር በቀል የውርደትና  የስቃይ ህይወት አልበቃ  ብሎ ወያኔ ከሳውዲ የጨለማ ዘመን ገዥዎች ጋር በመተባበር ወንድሞቻችን በሳውዲ አውራ ጎዳናዎች ላይ እንዲታረዱ እህቶቻችን በቡድን በተደራጁ የሳውዲ ጎረምሳዎች  እንዲደፈሩ ሁኔታዎችን አመቻችቶ  ለኢትዮጵያውያን ያለውን እጅግ የከረረ ጥላቻ በአደባባይ ያሳየበት አመት ነው። እንዲህ አይነቱ የጅምላ ግፍና  ውርደት ከመከሰቱ በፊት ህዝባዊ ሃይሉ በአረብ ሃገር በባርነትና  በስደት የሚገኙ እህትቶቻችንን ወንድሞችችን ስቃይ  ስቃዩ አድርጎ በመውሰድ “ላንቺ ነው” በሚለው ድርጅታዊ መዝሙሩ “በባለጌ  አረቦች መዳፍ ውድ ክብራቸው ለጎደፈው እህቶቻችን፣ በአረቦች የባርነት ቀንበር ጀርባቸው ለጎበጠው  ወገኖቻችን እንደርስላችኋለን፣ የተሰባሰብነው  ደማችን የሚፈሰው የመከራ ቀናችሁን ለማሳጠር ነው” የሚል ቃል ኪዳኑ ሰጥቶ  ነበር። የድርጅታችንን ምስረታ አንደኛ  አመት ስናከብር ልባችንን ደስታ ሳይሆን ሃዘን እንዲሞላ የሚያደርገው ይህ ቃል ኪዳናችን ለማክበር የጀመርነው ጉዞ ከድርጅት ምስረታና ከድርጅታዊ ዝግጅት አልፎ   በኢትዮጵያ ህዝብ ጥላቻና ንቀት  የተነፋውን የወያኔን እብሪት በማስተንፈስ የወሰዳቸው ተጨባጭ የአለኝታነት እርምጃዎች ባለመኖራቸው ነው።
ምንም እንኳን ግንቦት7 ህዝባዊ ሃይል እራሱን እንደ ድርጅት አቁሞ  ኢትዮጵያውያንን አሰባስቦ  መራራው ትግል የሚጠይቀውን የፖለቲካ  የወታደራዊ ስልጠናና ትጥቅ አስታጥቆ  በወያኔ  ላይ ለመዝመት የጀመረውን ጉዞ የሚያስቆመው ምድራዊ ሃይል እንደሌለ ብናውቅም የህዝብ ስቃይ ለግዜው መቀጠሉ የህባዊ ሃይሉን አባላት ማሰቃየቱ አልቀረም። በወያኔ  ግፈኛ አገዛዝ የተንገፈገፈው ወገናችን ህዝባዊ ሃይሉ የወያኔን አገዛዝ እድሜ  የሚያሳጥሩ ፈጣን እርምጃዎችን እንዲወስድ በከፍተኛ  ጉጉት እየተጠባበቀ እንደሆነ  እናውቃለን። ህዝባዊ ሃይሉን ለመቀላቀል በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ የሃገሪቱ ዜጎች በተጠንቀቅ እንደቆሙ እናውቃለን። እነዚህ ዜጎች ከሁሉም የእምነት የቋንቋ  የጾታ የእድሜ  የኑሮና  የማህበረሰብ ስብጥር የሚያካተቱ  እንደሆኑ እናውቃለን። በሃገሪቱ ታሪክ ተሰምቶና  ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ  የወታደር ልብሱን  እየጣፈ እንዲለብስ፣  የወታደር ጫማውን መቀየሪያ አጥቶ  ሸበጥ እንዲያደርግ የተገደደውን፣  የወያኔ ጀነራሎች በስልጣንና  በዘረፋ ሲያብጡ በድህነት እንዲሟሽሽ የተፈረደበት የሃገሪቱ ሰራዊት በዘር በእምነት ሳይለያይ ከህዝባዊ ሃይሉ ጎን ለመቆም አሰፍስፎ  የቆመ  እንደሆነ  እናውቃለን። ይህ ሃገራዊ እውነታ ለህዝብ የገባነውን ቃልኪዳን የለምንም ጥርጣሬ  ማስከበር እንደምንችል በሙሉ ድፍረት እንድናውጅ የሚያስችለን ሃቅ ነው።
የወያኔ ጀንበር እየጠለቀች የኢትዮጵያ  ህዝብ ጀንበር እየፈካች የመሄዱ ጉዳይ እንደማይታጠፈው  የመንጋትና  የመምሸት የተፈጥሮ ህግ ነቅነቅ የማይል እንደሆነ ግንቦት7 ጠንቅቆ ያውቃል።  እውቀታችን ልዩ ጥበብ የሚጠይቅ ኣይደለም። ግፍ ፍትህን አሸንፎ፣ እውነት በሃሰት ተደፍቃ፣ ጥላቻ ፍቅርን፣ አድሎ እኩልነትን፣ ሃገራዊ ክህደት ሃገር መውደድን፣ ባንዳነት አርበኛናትን ለዘላላሙ ቀብረው የሄዱበት የሃገራችንና  የሰው ልጆች ታሪክ የለምና የወያኔን አይቀሬ ሞት ለመተንበይ  ልዩ ጥበብ አያሻንም። ይህን እኛ ብቻ ሳንሆን በዘረፋና በጥላቻ  የደነዘዘ ህሊና ያዳበሩት የወያኔ  ባለስልጣናትም ያውቁታል። ያለእኔ  ጀግና የለም፣ ያለእኔ  አልሞ  ተኳሽ የለም በሚል እብሪት በመጻደቅ የሚታወቁት ወያኔዎች በመቶ ሽዎች በሚቆጠሩ ወታደሮች ተከበው፣  በታንክ በአይሮፕላን በሚሳይል ታጅበው ከሚኖሩበት ቤተመንግስትና ቪላዎች ውስጥ ብርክ እንዲይዛቸው ያደረገው ለመሆኑ፣  ሳር ቅጠሉ ግንቦት ሰባት እየመሰላቸው ሲበረግጉ እንደሚያመሹ፣  የግንቦት ሰባት አባላት እያሉ ከድርጅታችን ጋር አንዳችም ግንኙነት የሌላቸውን ዜጎች እያሰሩ ሲያሰቃዩ ፣  ከምላሳቸው ላይ ግንቦት 7  የሚል ስም ተፈናጦባቸው  እንደሚውሉ በራሳቸው ሚድያ  ወያኔዎች ራሳቸው እያሳዩን እያስደመጡን ነው። ከዚህም አልፎ በዚህ አንድ አመት ውስጥ  የህዝባዊ ሃይሉን መሪዎች በመግደል ድርጅቱን ለማኮላሸት ይቻላል በሚል ወያኔ የላካቸው ነፍሰ ገዳዮችና ድርጅቱን ከውስጥ ለመቦርቦር ያሰማራቸው ሰርጎገቦች ተራ በተራ ተልእኳቸው እየከሸፈ በህዝባዊ ሃይሉ እጅ እየወደቁ ወይም ተልእኳቸው እንደማይሳካ ሲረዱ እየፈረጠጡ ወደ ወያኔ ሲመለሱ አይተናል።
ያለፈው አንድ አመት ተመክሯችን ስለወያኔ  ብቻ ሳይሆን ስለራሳችንም ጥንካሬና  ድክመት ብዙ ነገሮች ያስተማረን ኣመት ነው። የቀደምቶቻችን የጀግንነት የአርበኛነት ቅርስ በመላ ህዋሳቸው የተሸከሙ  ለኢትዮጵያ እና  ለህዝቧ ሲሉ ደማቸው ለማፍሰስ ውድ ህይወታቸውን ለመሰዋት ወደኋላ የማይሉ ቆራጥ ብቻ ሳይሆኑ አርቀው የሚያዩ  በርካታ ልጆች  ሃጋሪቷ ያሏት መሆኑን ያረጋገጥንበት አመት  ነው።  በሌላ በኩል ደግሞ  ድርጅታችን የኢትዮጵያን ህዝብ ብቸኛው የመንግስት ስልጣን ባላቤት የማድረጉን ታሪካዊ ራእዩን ለመሳካት የሚያደረገው ትግል ከወያኔ ጋር ብቻ ሳይሆን ከራሳችንም ጋር የሚደረግ እንደሆነ  በሚገባ  የተረዳነው  በዚሁ የአንድ አመት የድርጅታችን እድሜ  ነው። ከራሳችን ጋር የሚደረግ ትግል ወያኔ በማህበረሰባችን ውስጥ ከዘራቸውና የሃገሪቱን ዜጎች እንዲበክሉ ካደረጋቸው የዘረኛነት የአድሎ  ከህዝብና  ከሃገር ጥቅም በፊት የራስን ጥቅም ማስቀደም፣ የሱሰኛነትና የሙስናና ሌሎችም አደገኛ ባህሎች ጋር ነው።
ህዝባዊ ሃይሉ ደግሞ  ደጋግሞ  እንደገለጸው ትግላችን አንድ መንግስታዊ ስርአት ወድቆ ሌላው የመንግስት ስርአት በመጣ ቁጥር የህዝብ ተስፋ እየጨለመ  “አዲስ ከመጣው ስርአት ያላፈው ያረጀ ስርአት በግፈኛነቱ በዘራፊነቱ ያነሰ ነበር” የሚል የግፈኛና የዘራፊ ስርአቶች ንጽጽር ላይ የቆመ አሳዛኝ የህዝብ ህይወት እንዲያበቃ ነው። ደርግን ያየ የአጼውን ስርአት እንከኖች ረስቶ ንጉሱ ይሻሉን ነበር ያለበት፣ ወያኔን ያየ የደርግን አስከፊ ዘመን ረስቶ መንጌ በስንት ጣሙ ያለበት አሳዛኝ ሁኔታ ከወያኔ መውደቅ በኋላ በሃገራችን እንዳይደገም ነው ትግላችን። የኢትዮጵያ ህዝብ የውድ ልጆቹን ህይወት ገብሮ ወያኔን በማስወገድ የሚያመጣው ስርአት ከወያኔ ብሶ ህዝብ ወያኔ ማረኝ የሚልበትን ቅስም ሰባሪና አዋራጅ የታሪክ ቅጥልጥሎሽ  እንዳይቀጥል ማድረግ ህዝባዊ ሃይሉ የተመሰረተበት፣ አባላቱ መከራ ለመቀበልና መስዋእትነት ለመክፈል በረሃ የገቡበት ዋናውና ብቸናው ምክንያት ነው። ትግላችንን መራራ የሚያደርገው ከበሰበሰውና የአንድ ጀምበር የህዝብ ቁጣ ከታሪክ ቆሻሻ የመጠያ ስፍራ ከሚከምረው  የወያኔ ስርአት ጋር ብቻ ሳይሆን በወያኔ ቦታ የሚተካውን ስርአት ከአድሎና ከዘረኛነት ከዘረፋና ሃገራዊ ክህደት የጸዳ፣ ዳግም ለኢትዮጵያውያን ውርደትና እንግልት ምክንያት እንዳይሆን ለማድረግ ከራሳችን ጋር ሳይቀር የማያቋርጥ ትግልን ማድረግ የግድ ስለሚል ነው። ህዝባዊ ሃይሉ የአመጽ ትግል የሚያደርግ፣ የመሳሪያው ብዛትና  የሰራዊቱ ቁጥር እያደገ  የሚሄድ ሃይል መሆኑን ስለምንረዳ  ይህን ሃይል ገና ከጅምሩ ከብዙ እንከኖች እያጸዱ ማደራጀት ካልተቻለ  በሃገርና በህዝብ ላይ የሚመጣውን አደጋ  የህዝባዊ ሃይሉ አባላት ጠንቅቀው የተረዱት ሃቅ ነው። ይህ ግንዛቤ የሰራዊቱን አባላት በጥንቃቄ መመልመልን፣ ማሰልጠንንና መገንባትን የግድ የሚል ነው።
ይህ ከራሳችን ጋር የሚደረግ ትግል እጅግ መራራ ነው። ታሪካዊ ስህተቶችን ላለመድገም የሚደረግ ትግል ነው። ይህ ትግል የአካልና የመንፈስ ጽናትን፣ ሃቀኛነትን፣ ታማኝነትን፣ ጀግንነትን የሚጠይቅ ትግል ነው። የወያኔ ስርአት ከሃገር ግድያው በተጨማሪ ትውልድን ለመግደል ሆን ብሎ ያስፋፋቸው እኩይና ጎጂ ባህሎችና ልምዶች ምን ያህል ማህበረሰባችንን እንደጎዱት ህዝባዊ ሃይሉ ባላፈው አንድ አመት እድሜው በሚገባ የተረዳው ጉዳይ ሆኗል። ህዝባዊ ሃይሉ የሚመኘውን የኢትዮጵያ ትንሳኤና ተሃድሶ እውን ለማድረግ እነኝህ  ወያኔ ሆን ብሎ  ያስፋፋቸውን የባህልና የሞራል ብክለት ማጽዳት የግድ እንደሆነ የተረዳ አካል ሆኗል።
ትግላችን መደፍረስን መጥራትን፣ መንተክተክን መስከንን የትግሉ ሂደት አካል አድርጎ  የሚጓዝ ነው።   ትግሉ የሚልመጠመጠውን እንደቀስት ቀጥ ብሎ ከሚራመደው፣ በካፊያው የሚንቀጠ ቀጠውን ለዶፉ ደንታ ከሌለው፣ ዝናር በቅፌን ከምሩ ተኳሽ  የሚለይ መራራ ትግል ነው። ያለፈው አንድ አመት ይህን አስተምሮናል። ህዝባዊ ሃይሉ ትግሉ ቀላል ነው የሚል ከእውነታ ጋር ያልተያያዘ ቃል ለህዝብም ሆነ ህዝባዊ ሃይሉን ሊቀላቀሉት ለተዘጋጁት ወገኖቹ አይናገርም። ህዝባዊ ሃይሉን ለመቀላቀል ለተሰለፉ በሽዎች ለሚቆጠሩ ወገኖቻችን ትግሉ የሚጠየቅውን የሞራል የስብእና ጥብቅነት፣ከፍተኛ  የሃገርና የወገን ፍቅር፣ ጥልቅ የሆነ የመስዋእትነት ፈቃደኛነት የሚጠይቅ መሆኑን ከማስረዳት አንቦዝንም። ህዝባዊ ሃይሉ ለህዝብ ቃል እንደገባው ከወያኔ  ጋር የምናደርገው ትግል በጥበብ በእውቀት በጥናት በጥንቃቄ የምናደርገደው ነው። ነጻነት ያለመስዋእትነት እንደማይሳካ ብናውቅም ለተራ የፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ስንል በቂ ዝግጅት ያልተደረገበት የሃገሪቱን ውድ ልጆች በከንቱ የሚማግድ ጀብደኛ እንቅስቃሴ  አናደርግም። የውሸት ተስፋ  ህዝብን አንመግብም።  አይናችንን ከዋናው የኢትዮጵያና  የህዝቧ  ጠላት ከሆነው ከወያኔ ላይ አንስተን በሌሎች  ወያኔን እቃወማለሁ በሚሉ ሃይሎች ላይ አንተክልም። ከወያኔ ሌላ ወደ ጎን የምንዋጋው፣ የምንጨቃጨው አታካራ የምንገጥመው ምንም ሃይል አይኖርም። ወያኔን ለመምታት ህዝባዊ ሃይሉ የጨበጠው  ቡጢ ወገኖቻችን በፍቅር ለመጨበጥ የሚዘረጉ ጣቶች  እንዳሉት በጸረ ወያኔ ዴሞክራሲያዊ ትግሉ  ከልባቸው ለመተባበር ለሚፈልጉ ሃይሎች ሁሉ ግልጽ እናደርጋለን።
ያለፈው አንድ አመት የመሰባሰብ የድርጅት ምስረታ  መሰረታዊ የሆኑ የፖለቲካና የወታደራዊ  ስልጠና የተሰጠበት፣ የድርጅት ማጠናከሪያና የማጥራት ሂደት የተካሄደበት ነው። በዚህ ረገድ የተሰራው ስራ አጥጋቢ ውጤት አስገኝቷል። ስልጠናው፣ ድርጅት ማጠናከሩና  ማጥራቱ ወደፊትም የሚቀጥል ነው። መጪውን አመት የተለየ የሚያደርገው ህዝባዊ ሃይሉ በህዝብ ላይ በሚደርሰው ግፍና ውርደት ከሚሰማው ከፍተኛ ብስጭትና ቁጭት አልፎ ባላፈው አመት ሊደርስላቸው ያልቻለውን የሃገራችንን ግፉአን ህዝቦች መታደግ የሚችልበትን እርምጃዎች መውሰድ የሚችልበት አመት መሆኑ ነው። በዚህ የህዝባዊ ሃይላችን የአንደኛ አመት ምስረታ  ክብረ በአል ወቅት ወገንም ጠላትም በግልጽ እንዲያውቀው የምንፈልገው ይህን ሃቅ ብቻ ነው።
ውድመት ለዋናውና  ለብቸኛው የኢትዮጵያ ህዝብና  የኢትዮጵያችን ጠላት ለሆነው የወያኔ ገዥ ጉጅሌ!
ድል በወያኔ ግፈኛ ስርአት አበሳውን ለሚያየው የመላው የኢትዮጵያ  ህዝብ!
የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል

Monday, December 16, 2013

ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ በኖርዎይ በርገን ከተማ በደመቀ ሁኔታ ተካሔደ

በበርገን ከተማ ለመጀመርያ ግዜ በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዎይ  በርገን ቅርንጫፍ አስተናጋጅነት በዲሴምበር 14፥2013 የተዘጋጀው ህዝባዊ ስብሰባ በደመቀ ሁኔታ የተጠናቀቀ ሲሆን ከ100 በላይ የሚገመት ህዝብ የተገኘ ሲሆን ከተለያዩ የኖርዎይ ከተሞች የተሰባሰቡ ኢትዮጵያውያን በዝግጅቱም ላይ ተገኝተዋል፥፥
በዝግጅቱ ላይ ተጋባዥ እንግዶች የነበሩት
1ኛ. ዶ/ር ታደሰ ብሩ የግንቦት7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ስራ አስፈጻሚ አባል
2ኛ. አቶ ዮሃንስ አለሙ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዎይ  ዋና ሊቀመንበር
3ኛ. ዶ/ር ሙሉአለም አዳም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ በኖርዎይ የድርጅት አባል ናቸው፥፥
የውይይት መድረኩ ከመጀመሩ በፊት በሳውዲ አረቢያ እየተሰቃዩ፥ እየተገደሉ እንዲሁም በግፍ ኢሰብአዊ ድርጊት ለተፈፀመባቸው ወገኖቻችን የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ የተጀመረ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዎይ  የበርገን  ቅርንጫፍ ጽ/ት ሰብሳቢ አቶ ሹሜ ወርቁ አጭር የመክፈቻ ንግግር ካረጉ በኋዋላ ተጋባዥ እንግዶቹ በየተራ ስለሚመሩአቸው ድርጅቶችና የወቅቱን የሃገራችንን አስከፊ የፖለቲካ ሁኔታ በተመለከተና ሁሉም የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች አብረው በስምምነት የሚሰሩበትን ሁኔታ ማምጣት እንዳለብን እንዲሁም ስለ  መደራጀት አስፈላጊነት ሰፋ ያለ ማብራርያ  ሰጥተዋል፥፥
ዶ/ር ታደሰ ብሩ ስለ ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዓላማ ራእይና ግብ እንዲሁም ስለውጭ እምቢተኝነት ሰፋ ያለ ማብራሪያ ከሰጡ  በኋላ ሁሉም ኢትዮያዊ ግንቦት7ትን እንዲቀላቀልና ሃገራችን ኢትዮጵያ ከገባችበት አዘቅት ውስጥ ተባብረን እንታደጋት በማለት  ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በተለያዩ ድርጅቶች ስር ተደራጅቶና ታቅፎ መንቀሳቀሱ ያለውን ጠቀሜታና የሐይማኖትና የሲቪክ ማህበራትን ማደራጀትና ማጠናከር ጠቃሚ መሆኑን አሳስበዋል፥፥ ፥፥
 አቶ ዮሃንስ አለሙ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዎይ  ዋና ሊቀመንበር ስለ ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ አመሰራረትና የደረሰበትን ደረጃ እንዲሁም ያከናወናቸውን ተግባራት በተመለከተ በሰፊው ገለጻ  ያደረጉ ሲሆን  ከህዝቡም  ለቀረበላቸው ጥያቄም  ምላሽ ሰጥተዋል፥፥
በተጨማሪም ዶ/ር ሙሉዓለም አዳም በኖርዎይ የስደተኞች አኗኗር ዙሪያ ያለውን ችግር እንዲሁም ሁሉም የተቃቃሚ ድርጅቶች አንድ ላይ ሆነው እንዲሰሩ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን በመጨረሻም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዎይ የበርገን ቅርንጫፍ በተቋቋመ በአጭር ግዜ ውስጥ የደረሰበት ደረጃም በእጅጉ አስደሳች እንደሆነ በመግለፅ ያላቸውን አድናቆት ገልጸው ህዝቡ ለነጻነት ለሚደረገው  ትግል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል፥፥
እንዲሁም በዝግጅቱ ላይ በሐና ሰመረ ሐቅ ተሰደደ በሚል ርእስ አጭር ግጥም የቀረበ ሲሆን በመቀጠልም በሎሚታ ገብረሚካኤል በምስል በተደገፈ በቀረበው የኢትዮጵያ የታሪክ ጉዞ ከነገስታት ስርአት እስከ ሐገራችን በወያኔ አገዛዝ ስር ወድቃ አሁን የደረሰችበትን ሁኔታ የሚያሳይ ዘገባ ለታዳሚው ቀርቧል፥፥
በመጨረሻም ለእንግዶቹ የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርቦ ውይይት ከተደረገ በኋላ ዝግጅቱ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሐይል መዝሙርን በመዘበር በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፥፥
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዎይ  የበርገን  ቅርንጫፍ ጽ/ት
ዲሴምበር 14፥2013

Sunday, December 15, 2013

14 ህፃናት ከመኪና ቃጠሎ ተረፉ

14 ህፃናት ተማሪዎችን አሳፍሮ ከጎተራ ወደ ካቴድራል ትምህርት ቤት ይጓዝ በነበረ ኩምቢ ቮልስ መኪና ላይ ባልታወቀ ምክንያት በተነሳ እሳት ሙሉ በሙሉ የወደመ ሲሆን በህፃናቱ ላይ ምንም አይነት አደጋ አለመድረሱ ታውቋል፡፡ ጎተራ ማሳለጫ ላይ ከመኪናው የፊት አካል የተነሳውን እሳት የተመለከተው ሹፌሩ፤ ልጆቹን ፈጥኖ ከመኪናው በማውጣቱ በህይወት ላይ አደጋ አለመድረሱን የጠቆመው ፖሊስ፤ መኪናው በምን ምክንያት ለእሳት ቃጠሎ እንደተዳረገ የቂርቆስ ፖሊስ መምሪያ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አመልክቷል፡፡ እሳቱ በምን እንደተነሳ የተጠየቀው ሹፌሩ፤ እሱም ምክንያቱን እንደማያውቅ ተናግሯል፡፡ ስለ አደጋው ያነጋገርናቸው የእሳትና ድንገተኛ አደጋ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ በበኩላቸው፤ መኪናው 8 ሰው ብቻ መጫን ያለበት ቢሆንም 14 ህፃናት አሳፍሮ እንደነበር ገልፀዋል፡፡ እሳቱን ለማጥፋት ከ25 ሺህ ሊትር በላይ ፈሳሽ እንደፈጀና መኪናው በቃጠሎው ከጥቅም ውጭ እንደሆነ አቶ ንጋቱ ገልፀዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከ600 በላይ አባዎራዎች ቤታቸውን በ3 ቀናት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ ቀጭን ትዕዛዝ ተላለ

የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት ደሃ ገበሬዎችን እያፈናቀሉ ቦታቸውን እየወሰዱ ነው

በአዲስ አበባ ከ600 በላይ አባዎራዎች ቤታቸውን በ3 ቀናት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ መታዘዛቸውን ኢሳት ቴሌቭዥን ዘገበ። እንደ ቲቪው ዘገባ ትእዛዙን የሰጠው የቦሌ ክፍለከተማ ሲሆን፣ ነዋሪዎቹ እስከ ማክሰኞ ቤታቸውን ለቀው ካልወጡ ፣ አፍራሽ ግብረሀይል በጉልበት እንደሚያፈርስባቸው አስታውቋል።

“በሶስት ቀናት ውስጥ የት እንሄዳለን?’ ሲሉ የሚጠይቁት ነዋሪዎች ፣በአሁኑ ጊዜ በአዲስ አበባ የሚታየው የቤት ኪራይ መጨመር አስግቶናል ብለዋል። ሜዳ ላይ እንዃ እንዳንወድቅ ሜዳውም እየታረሰ ነው ሲሉ ነዋሪዎች ምሬታቸውን ገልጸዋል ሲል ዘግቧል።
በተያያዘ ዜናም ኢሳት በዜና ዘገባው በኦሮሚያ ልዩ ዞን የሚገኙ ባለስልጣናት በስልጣናቸው ደሀ ገበሬዎችን እያፈናቀሉ ቦታዎቻቸውን እየወሰዱባቸው ነው ሲል ዘገበ። ነዋሪዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው አርሶአደሮች በጉልበት መሬታቸውን እየተቀሙ ለበለጠ ድህነት እየተጋለጡ መሆኑን አስታውቋል። ከተቀሙት አርሶ አደሮች መካከል በሰበታ ነዋሪ ከሆኑት አንዱ ሲናገሩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሆኑት የአቶ ደምሴ ቡላ ባለቤት መሬታቸውን በጉልበት እንደነጠቁዋቸውና ክስ ሲመሰርቱም እንዳሳሰሩዋቸው ተናግረዋል ያለው ኢሳት በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ቤት ሰርተው ይኖሩ ነበሩ ሰዎች ቤቶቻቸው ከፈረሱባቸው በሁዋላ ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸው ይታወቃል ሲል የዜና ዘገባውን አጠቃሏል።

Friday, December 13, 2013

ጄነራል ሳሞራ የኑስ በውጭ ተቃዋሚዎች የመለስን የበላይነት መስክረዋል አሉ

(ዘ-ሐበሻ) ኢሕአዴግ ለይስሙላ ያከብረዋል እየተባለ በሚተቸውና ለ8ኛ ጊዜ የተከበረውን የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች የሕገ መንግሥት ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ መንግስት ባሳተመው ‘ሕብረ ብሔር’ መጽሔት ላይ ቃለ ምልልስ የሰጡት የጦር ኃይሎች ኤታማዦር ሹም ጀነራል ሳሞራ የኑስ መለስ ከሞተ በኋላ በውጭ ያሉ ተቃዋሚዎች የሟቹን አቶ መለስ ዜናዊን የበላይነት መስክረዋልና እናመሰግናቸዋለን አሉ። በሰራዊቱ ውስጥ እኩልነት እንዳለ መናገራቸውም ብዙዎችን አስገርሟል።

በከፍተኛ ህመም እየተሰቃዩ ነው በሚል በተደጋጋሚ ተጽፎላቸው የነበሩትና አሁንም ህክምና ሁልጊዜ እንደሚከታተሉ የሚነገርላቸው ጄነራል ሳሞራ ከመንግስታዊው መጽሔት “የቀድሞው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ህልፈተ ሕይወታቸው በድንገት ከተሰማ በኋላ በውጭ የሚገኙ አንዳንድ ፀረሰላም ኃይሎች እና አንዳንድ ተቃዋሚዎች ኢትዮጵያ ለሽብርና ለሌሎች ፀረ-ሰላም ተግባር መጋለጧ አይቀርም ሠራዊቷም መዳከሙ አይቀርም በማለት ሲገልጹ ነበር። ይህ ሊሆን ያልቻለው ለምንድ ንነው ይላሉ? እነዚህ ወገኖች ይህን ተመኝተዋል ነገር ግን ያልሞከሩት ከምን አንፃር ነው?” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ “ከመለስ በኋላ ሠራዊቱ ይዳከማል ብለው ማሰባቸው የመለስ አስተዋፅኦ ጠንካራ ሠራዊት እንዲኖር፣ ጠንካራ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ኃይል እንዲኖር ያስቻለ ስለመሆኑ እውቅና መስጠት ስለሆነ እናመሰግናለን።” ካሉ በኋላ ቀጥለውም “ምክንያቱም መለስ ይህቺ አገር ጠንካራ የመከላከያ ኃይል እንዲኖራት ወሳኝ ድርሻ ነበረው ብለው ስላመኑ ነው ይህንን ማንሳት የጀመሩት፡፡ ይህን ማሰብ በመጀመራቸው ደግሞ መመስገን ይኖርባቸዋል፡፡” ብለዋል።
ሳሞራ በመንግስታዊው ጋዜጠኛ ለቀረበላቸው ለዚሁ ተመሳሳይ ጥያቄ በሌላ በኩል የአንድ ሰራዊት ጥንካሬ የሚለካው በሰራው አንድ ሥራ ብቻ አይደለም። ሠራዊቱ ይህቺ አገር እስካለች ድረስ አብሮ ይኖራል። ምክንያቱም ተቋሙ ቀጣይ ነው። ተቋሙ ለሁለት ነገር ብቁ መሆን አለበት። አንደኛ ለወቅታዊ ግዳጁ፣ ሁለተኛ ደግሞ ለወደፊት ለሚሰጥ ግዳጅ ብቁና ዝግጁ መሆን አለበት። የእያንዳንዱ አመራር ተልዕኮም ይሄ ነው። በተለይ የከፍተኛ አመራሩ ተልዕኮ ይህንን ማረጋገጥ ነው። ይሄን እንዴት እንፈፅመዋለን ለሚለው ደግሞ ሶስት መሰረታዊ ሥራዎችን በመሥራት ነው።
ዋናውና ወሳኙ የሰው ኃይሉን ማዕከል ያደረገ ሥራ መሥራት ነው። የሰው ኃይሉን ማብቃት። ቴክኒካዊና ሙያዊ እንዲሁም አካዳሚያዊ ብቃቱን ማሳደግ፣ ሳይንሳዊ ዕውቀቱን ማዳበር፡፡ እንግዲህ ሶስት የአቅም ግንባታ ሥራ መሥራት ዋነኛው ሆኖ የሰው ኃይል ማዕከል ያደረገ የአቅም ግንባታ ሥራ መስራት ያስፈልጋል። ሁለተኛው ሥራ በአደረጃጀቱና አሰራሩ ሕዝባዊ ባህሪውን እንደጠበቀ ከተልዕኮውና ከባህሪው የሚስማማ አደረጃጀትና አሰራር ያለው እንዲሆን ማድረግ ነው። አደረጃጀት አቅም ፈጣሪ ነው። አደረጃጀት ለዘለዓለም የሚኖር አይደለም። ከሁኔታው ጋር እየዳበረ አቅም እየፈጠረ የሚሄድ መሆን አለበት። አሰራሩም በተመሳሳይ ከሕዝባዊ ባህሪውና ከተልዕኮው የተጣጣመ አሰራር ዴሞክራሲ ያዊና ደስተኛ ሕይወቱን በአስተማማኝ የሚጠብቅ፣ የግዳጅ አስተሳሰቡንና ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰቦችን የሚያዳብሩ አሰራሮችን ማረጋገጥ ማለት ነው። አደረጃጀቱም፣ አሰራሩም፣ የሰው ኃይሉም ሦስቱን ሥራዎች በመሥራት ነው ለተጨባጭ ግዳጅም ሆነ ለወደፊት ለሚሰጠው ግዳጅም ዝግጁ የሚሆነው፡፡
“ስለዚህ ሠራዊቱ በዚህ እየተገነባ ስለቆየ ነው ውጤትም እየተገኘ የመጣው፡፡ ካብ አይደለም ሲሠራ የነበረው። ጠንካራ የመከላከያ ተቋም፣ ጠንካራ የመከላከያ ኃይል፣ ሕዝባዊ ባህሪውን የጠበቀ የመከላከያ ኃይል ነው ሲገነባ የነበረው። እና በዚህ ምክንያት ሊፈርስ አልቻለም፡፡ አይፈርስምም ይጠነክራል።
እነዚያ ወገኖች የተመኙትን አልሞከሩትም ማለት ግን አይደለም፡፡ የብተናና የተለያዩ ሥራዎችን አልሞከሩም ማለትም አይደለም። መከላከያ ሠራዊታችንን የሚያፈርሱት ሦስት ምክንያቶች ካጋጠሙ ብቻ ነው የሚል እምነት አለን። በንግግር አይፈርስም። በሦስት ነገር ግን ሊፈርስ ይችላል። አንደኛውና ዋናው ተልዕኮው ከተቀየረ ነው፡፡ እንግዲህ አሁን ተልዕኮው ሕዝባዊ ነው። የወረራ ተልዕኮ የለውም። የሠላም ተልዕኮ ነው ያለው፡፡ ምክንያቱም የኢትዮጵያ ህዝብ ተስፋው ከሰላም እንጂ ከጦርነት አይደለም፡፡ ስለዚህ ከዋናው ተልዕኮ አንደኛው ሠላም ማረጋገጥ ነው። ይህ ደግሞ በሕገ መንግሥቱ የተቀመጠለት ነው። ሁለተኛው ደግሞ የጦርነት አደጋ ካጋጠመ በአጭር ጊዜ እና በአስተማማኝ በመጨረስ ተመልሰን ወደ ልማታችን መግባት ነው።ሌላው ተልዕኮ ደግሞ የአፍሪካ ወንድሞቻችን ከእኛ ለሚፈልጉት ሁሉ አስፈላጊውን ድጋፍ ማበርከት ነው።
የእነርሱ ሰላም የእኛም ሰላም ስለሆነ በአቅማችን በሰላም ማስከበር ሥራ መሳተፍ ነው። አራተኛው ደግሞ በአገር ውስጥ ከፀጥታ ኃይሎች አቅም በላይ የሆነ ጉዳይ ካለ መሳተፍ። በህብረተሰቡ ላይ ሰብአዊና ተፈጥሮአዊ አደጋዎች ከአጋጠሙ የድርሻችንን መወጣት ነው። እነዚህ ተልዕኮዎች ሕዝባዊ ተልዕኮዎች ናቸው። ከሕገ መንግሥቱ የወጡ፣ የተቀዱ ተልዕኮዎች ናቸው።
“ሁለተኛው የሠራዊቱን ጥንካሬ ሊበረብር የሚችል ደግሞ የራሱ የሰራዊቱ የውስጥ ችግር ነው። ኢ-ዴሞክራሲያዊነት ከሰፈነ ሠራዊቱን ሊያፈርሰው ይችላል። ኢ-ዴሞክራሲያዊነት ከተፈጠረ በርካታ መዘዞች ይመጣሉ። ፀረ-ዴሞክራቲክ መሆን ከተጀመረ የህግ የበላይነት ይጣሳል ማለት ነው፡፡ በአንድ በኩል በህግና በአሰራር መሄድ ይቀራል። ሁለተኛ የሠራዊቱ ደስተኛና ዴሞክራሲያዊ ሕይወት ይበላሻል። ስለሆነም ጠንካራ አንድነት፣ አስተማማኝ አንድነት፣ የማይናወጥ አንድነት ያለውን ሠራዊት አንድነቱ እንዲናጋ ያደርገዋል። የጌታና የአሽከር አካሄድ ነው የሚኖረው፡፡ ይሄ ደግሞ ለአገሪቱም ለሁሉም አይጠቅምም።
“ሌላው ደግሞ ሙስና ነው። ሙስና ሠራዊቱን ሊያበላሸው ይችላል፡፡ ሙስና ፀረ ልማት ነው። ሠራዊቱን ሊበትነው እና ሕዝባዊ ባህሪውን እንዲያጠፋ ሊያደርገው ይችላል። አንድ ሠራዊት ሠራዊት ነው የሚባለው እንደ ወታደር እንደ አንድ አካል ሲያስብ እንጂ ለግሉ ሲያስብ አይደለም።
ለምሳሌ አንድ ወታደር በአንድ ሻለቃ ወይም በአንድ ቡድን ሊድን ከሆነ ሻለቃዋ መዳን አለባት፡፡ በሌላ በኩል አስሩ ከዳኑ ነው እርሱ መዳን የሚችለው። ቡድኑ ብቻውን ሊድን አይችልም። ስለዚህ ይሄ ሻለቃ አስሩን ማዳን አለበት።ወታደሩ መዳኑ የሚረጋገጠው አስሩ ከዳኑ ይሆናል። ብቻውን ሊድን ከፈለገ አይችልም። በተመሳሳይ አንድ የመቶ ካለችም ሶስት ቲም አሏት፡፡ የመቶዋ ልትድን ከሆነ ቲሟ መስዋዕትነት መክፈል አለባት፡፡ እንደዛ እያለ ነው የሚሄደው፡፡ ስለዚህ እንደ አንድ አካል የሚያስብ መሆን አለበት፡፡ ፀረ ዲሞክራሲ አካሄድ ካለ በውስጡ አንድነቱ ይላላል፤አስተሳሰቡም ይሸረሸራል ማለት ነው፡፡ ሙስናም በተመሳሳይ ለግል ማሰብን ይመጣል፤ ይህም ያፈርሰዋል። በአጠቃላይ በዚህ ነው የሚፈርሰው እንጂ በንግግርና በአሉባልታ አይደለም።” ብለዋል።
የአንድ ብሔር ተወላጆች በሰራዊቱ ውስጥ ቁልፍ ቦታ መያዛቸው፣ በትውልድ ብሔራቸው የተነሳም በሙስና ነቅዘው ሃብታም መሆናቸውን፣ መከላከያ ሰራዊቱም የሃገር ዘራፊዎች መሳሪያ መሆኑን በስፋት በሕዝብ ዘንድ የታወቀ ሆኖ ሳለ ኤታማዦር ሹሙ ይህንን ሽምጥጥ አድርገው በመካድ ለዚሁ መጽሄት “ወታደር ሲሆን ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን የመጠበቅ ተልዕኮ ነው ያለው። ሌላ ምንም ነገር የለውም። ከሌላው ዓለም የእኛ ደግሞ ትንሽ ይለያል። ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱ የሚጠበቀው በሕዝቡ፣ በሠራዊቱም በሁሉም እኩል ነው፡፡ የሁሉንም ሕዝቦች ተጠቃሚነት ስለሚያረጋግጥ በተወሰኑ ምሁራን ብቻ የሚጠበቅ አይደለም፡፡ስለዚህ የሁሉንም ህዝቦች ተጠቃሚነት የሚያረጋግጠውን ህገመንግስት ሁሉም ህዝብ ማወቅ አለበት፡፡ ሁሉም ህዝብ ማወቅ አለበት ብቻ ሳይሆን እንዲያምንበትም መደረግ መቻል አለበት፡፡ካመነበት በኋላ ደግሞ እንደወታደር ለመጠበቅም ለመስዋዕት ራሱን ዝግጁ እንዲያደርግ ይገነባበታል።” ማለታቸው ትዝብት ውስጥ እንደጣላቸው ታዛቢዎች ይናገራሉ።

Wednesday, December 11, 2013

ኢትዮ-እስራኤላዊቷ የፓርላማ(የክኔሴት) አባል ፕኒና ታምኑ እሸቴ ዛሬ በ እስራኤል ፓርላማ በተደረገው የደም ልገሳ ፤ ደም መለገስ አትችይም ተባለች

ኢትዮ-እስራኤላዊቷ የፓርላማ(የክኔሴት) አባል ፕኒና ታምኑ እሸቴ ዛሬ በ እስራኤል ፓርላማ በተደረገው የደም ልገሳ ፤ ደም መለገስ አትችይም ተባለች ። የጤና ሚንስተር ዶ/ር ጌርማን ” .ይህ አይነቱ እኩልነት የጎደለው ድርጊት በ 2013 ዓ.ም በ እስራኤል በመፈፀሙ በጣም አዝናለሁ ” ሲሉ ለኢትዮ_እስራኤላዊቷ የፓርላማ አባል ፕኒና ታምኑ እሸቴ ከልብ ማዘናቸውንና ለወደፊቱም በ እስራኤል ፓርላማ ነገሮችን ለማሻሻል አብረው መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል  ፤ ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ  http://www.clickhabesh.com/?p=103901

በጅዳ ቆንስል በር ውላ የምታድረው እህት ክራሞት...

December 11, 2013

ነቢዩ ሲራክ
Ethiopian woman in Saudi Arabia, Jiddah Ethiopian embassy
ይህችን እህት በጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት በር ተቀምጣ ካየኋት ሳምንት አልፏል። አልፎ አልፎ ላነጋግራት ብሞክርም መልስ አትሰጥም። መጀመሪያ ያየኋት ቀን አካባቢ ከስራ ለተፈናቀሉ እህቶች አነሰም በዛ መጠለያ እያለ ፣ ለምን በር ላይ ትሆናለች? ብየ የጠየቅኳቸው የቆንስሉ ጸጥታ አስከባሪ “አንተየ የዚህች እህት ጉዳይ አስቸጋሪ ነው ። ከመጠለያው ብዙ ቆይታለች ፣ አሁን በር ላይ የሆነችው ሃገር ቤት ለመሄድ ወረቀቷ አልቆ እያለ “ሃገር ቤት አልሄድም!” በማለቷ እነረደሆነ ተነግሮኛል ። “በመጠለያው የነበሩት ሰነዳቸው ባሳር በመከራ አልቆ ሲሸኙ ወደ ሃገር ቤት አልሸኝም ብላ ረብሻ ከማንሳት አልፎ ከተዘጋጀው መኪና ወርዳ ይህን የምታየው ሚኒባስ መስታውት ሰብራዋለች! ከዚያን ቀን ወዲህ አትበላም አትጠጣም ፣ እኛንም የገረመን ይሄ ነው! ምን ታደርጋለህ! ” ነበር ያሉኝ …
ይህ ከተነገረኝም “ወዲህ ሃገር ቤት አልገባም!” ያለችው እህት ለቀናት በቆንስሉ በር አልጠፋችም። ከተቀመጠችበት ወንበር ጀርባ ባለው ግድግዳ “ህጋዊ ሰነድ የሌላችሁ እና የወጣውን የሳውዲ ህግ መስፈርት የማታሟሉ ወደ ሃገር ግቡ !” የሚለው የቆንስል ማስታወቂያ ይታያል ። ከአጠገቧ በፕላስቲክ ኪስ የታጨቀ ጓዟን አስቀምጣ ፣ በሆዷ ቁርአን ታቅፋ አንገቷን ከመድፋት ባለፈ በአካባቢው አዛን ስትሰማ የዘወትር ጸሎቷን (ሰላቷን) ወንበሯን ፈቀቅ አድርጋ እንደምትሰግድ አንድ ዘወትር እንቅስቃሴዋን የሚከታተል ወዳጀ አጫውቶኛል… እንዲህ ሆና ኮርመት ብላ ውላ ታድራለች! ቀን ጸሃይ ሲወቃት ፣ ማታ ወበቁ ይፈራረቅባታል ! ካየኋት ቀን ጀምሮ ወደ መጠለያው እንድትገባ ብዙ ሁነን ብንማጸናትም አልተሳካልንም …
ከሃገሯ በጤና የመጣችው እህት ችግር ውጋቷን እንድንጋራ ስንጠይቃት አትመልስም! ወደ ሃገር ቤት እንድትገባ በጅዳ ቆንስል ልትሸኝ ቢሞከርም አልተሳካም። የ”ሃገር ቤት ግቢ!” ” አልገባም!” አለ መግባባት ፍርሻ ከመምጣቱ በፊት አንዳንዴ ኦሮምኛና ብዙ ጊዜ ግን የተሰባበረ አረብኛ እየቀላቀለች መናገር ይቀናት እንደነበር አንድ “በመጠለያው እያለች አውቃታለሁ!” ያሉ ወንድም አጫውተውኛል። ያን ሰሞን ወደ መጠለያው እንድትገባ ተለምና ብትገባም በመጠለያው ውስጥ ካሉ ግፉአን ጋር ግብ ግብ ፈጥራ መውጣቷን ሰምቻለሁ!
ይዚህች ግፉዕ እህት ሰላም የነሳና አዕሮዋን ያወከ የውስጥ ህመም ሚስጥር አይታወቅም! ትሰማለች ፣ ለመናገር አልፈቀደችም! ባሳለፍናቸው የበር ላይ ውሎዋ ትንፍሽ ብላ ስትናገር ቢያን እኔ እስከ ዛሬ አልሰማኋትም ! ውስጧ እንጅ ውጭ አካሏ የተጎዳ አይመስልም! ከሁሉም የሚገርመው ይህች እህት ጤናዋ ታውኮ እንኳ ሃገር ቤት ከወገኖቿ ጋር መቀናቀል ሞት መስሏታል ! ሌላው አስገራሚ ሂደት የዚህችን መልከ መልካም እጣ ፈንታ የምንመለከትም ህጋዊ ሰነድ የሌለን ብዙዎች የሳውዲን መንግስት የምህረት ቀቢጸ-ተስፋ ሰንቀን ጤናችን ተጠብቆ እያለ” በሰላም ሃገር ቤት ግቡ!” የሚለውን የመንግስትና የወገን ምክር መቀበል አቅቶናል! እንዴት ነው ነገሩ …?
አንድየ ይታረቀን ከማለት ባሻገር ምን ይባላል :) ብቻ እሱ ያቅልለው እንጅ የሚሰማ የሚታየው ይከብዳል ! … ያማል … ያማል!

Tuesday, December 10, 2013

Saturday, December 7, 2013

ESAT Menalesh Meti ???

ESAT Menalesh Meti interview with Mr. Obang Dec 5 2013

http://ethsat.com/video/esat-menalesh-meti-interview-with-mr-obang-dec-5-2013/

ከሳውዲ ተመላሽ ዜጎች ንብረታቸው በጉምሩክ እንደተወሰደባቸው ተናገሩ

 7 בDecember 2013

ህገወጥ ናችሁ ተብለው ከሳውዲ አረቢያ ወደ አገራቸው የተመለሱ ኢትዮጵያዊያን፤ ለበርካታ አመታት ለፍተን ያፈራነውን ንብረት ይዛችሁ መግባት አትችሉም ተብሎ ተነጥቀናል፡፡ የፍተሻ ሰራተኞች 

radar_homeward_boundሻንጣዎቻቸውን በመፈተሽ፣ ሞባይል ከአንድ በላይ ከያዙ ትርፉን በማስቀረት፣ አዳዲስ አልባሳት እና ኤሌክትሮኒክስ ቁሰቁሶች የተወሰኑትን ብቻ በመፍቀድ እና ያመጡትን ወርቆች ግራም በመቀነስ ንብረታቸውን እየወሰዱባቸው እንደሆነ ተመላሾቹ ገልፀዋል፡፡ መሃመድ አባመጫ የተባለ የሳኡዲ ተመላሽ፤ ከሳውዲ ስድስት ሻንጣ ይዞ መምጣቱን ገልፆ፤ ቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርስ ግን ከሁለት ሻንጣ በላይ ይዞ መግባት እንደማይችል፣ ከአምስት ሞባይሎችም ሁለቱ ብቻ እነደተፈቀደለት ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ የሳውዲ መንግስት ከአንድ ኪሎ በላይ ወርቅ ይዛችሁ መውጣት አትችሉም የሚል መመሪያ ማሳለፉን የጠቆመው ተመላሹ፤ ንብረቱን እዚያው ጥሎ ለመመለስ መገደዱን ገልጿል፡፡ የሳኡዲ መንግስት እንኳን ከወርቅ በስተቀር ሌላ ንብረታቸውን ሁሉ ይዘው እንዲወጡ መፍቀዱን የገለፀው መሃመድ፤ በአገራቸው ንብረታቸውን እንዳያስገቡ መከልከላቸው እንዳሳዘነው ይናገራል፡፡
ኤሌክትሮኒክስና ለቤተሰቦቹ ያመጣውን ልብሶች ቀረጥ ከፍለህ ነው የምትወስደው በመባሉ፣ ለሁለት ቀን በስደት ተመላሾች በተዘጋጀው ድንኳን ውስጥ ያለምንም ፍራሽና ልብስ ተኝቶ ንብረቱን ቢጠብቅም ማግኘት እንዳልቻለ ገልጿል፡፡ “ሳዑዲም እዚህም ሀገራችን ስንደርስ እየበደሉን ያሉት ሃበሾች ናቸው” ያለው መሃመድ፤ መንግስት በሚዲያ በተሟላና በተደላደለ መንገድ እንደሚቀበለን ቢገልፅም እዚህ የጠበቀን ግን ሌላ ነው ሲል ቅሬታውን ገልፆ “ሌላው ቢቀር እስካሁን ተመላሾቹን የሚያመላልሰው እንኳን የሳዑዲ እንጂ የኢትዮጵያ መንግስት አይደለም” ብሏል፡፡ ከሳኡዲ ካመጣችው ወርቅ ላይ ሃምሳ ግራሙን ብቻ እንደምትወስድ የተነገራት ተኪያ ሙሃመድን ያገኘናት በቁጭት መሬት ላይ እየተንከባለለች ነበር፡፡
ተኪያ እያለቀሰች እንደነገረችን፤ ለ14 ዓመት ሰርታ ከሶስት መቶ ሃምሳ ግራም በላይ ወርቅ እንዳጠራቀመች ገልፃ፤ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከሳውዲ እንድትወጣ ከመገደዷ በፊት ሙሉ ንብረቷን አስቀድማ ብትልክም እስካሁን እንዳልደረሰላት ትናገራለች፡፡ አሁንም፤ ከተመለሰች በኋላ የያዘቻቸውን ሻንጣዎች ለመውሰድ እንዳልቻለች የምትገልፀው ተኪያ፤ በፍተሻ ስም ሰራተኞቹ ሻንጣዋን በርብረው በማየት፣ ያመጣቻቸውን የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችና ሶስት ሞባይሎች መውሰዳቸው ሳይንስ፣ ሶስት መቶ ግራም የሚመዝን የወርቅ ንብረቷን እንዳታስገባ መከልከሏን በጩኸት ትናገራለች፡፡ ለምን ንብረቷን እንደከለከሏት ስትጠይቅም “እናንተ ነጋዴዎች ናችሁ፤ በስደተኞች ስም ያለቀረጥ ንብረት ለማስገባት ትፈልጋላችሁ” በማለት ሰራተኞቹ እንደመለሱላት ገልፃ፤ ጉዳዩን ለአለቆቻቸው ለማመልከት ብትፈልግም የሚያናግራት ሰው አለማግኘቷን ጠቁማለች፡፡ በዚሁ ስፍራ ያገኘናቸው በርካታ ተመላሾች፤ የንብረታቸው ጉዳይ እንዳሳሰባቸው ይናገራሉ። ንብረታቸውን ሳይዙ ወደቤተሰቦቻቸው ላለመቀላቀል በሚል የተሰበሰቡበት ካምፕ፣ ምንም ለማረፊያ የተመቻቸ አገልግሎት ባለመኖሩ መቸገራቸውንም ገልፀዋል፡፡ መንግስት የሚሰጣቸውን 900 ብር፣ በትራንስፖርትና በስልክ አገልግሎት እንደሚጨርሱ አክለው ተናግረዋል፡፡
በርካቶች በእቃዎቻቸው መታገድ በመበሳጨታቸው ጭቅጭቅና አላስፈላጊ ውዝግብ ውስጥ ለመግባት መገደዳቸውን ተመላሾቹ ይናገራሉ፡፡ “ስንመጣ የሚሰጠንን ሊሴ ፓሴን አይተው ማስተናገድ ሲገባቸው እነሱ ግን ንብረታችንን እየወሰዱብን ነው” በማለት የሚናገሩት ተመላሽ ዜጎቹ፤ “ምናልባትም ንብረት የላቸውም ብለው አስበውን ይሆናል፤ ነገር ግን በርካታ አመታት ስንቆይ መቼም ባዶ እጃችንን አንመጣም” በማለት በምሬት ይናገራሉ፡፡ “ዛሬ እቃችንን የከለከሉን ነገ ምን ተስፋ ይዘን ነው ተደራጅታችሁ ስራ ስሩ ለሚሉን?” የሚሉት እነዚህ ተመላሾች፤ “በመንግስት ላይ አመኔታ የጣልነው ሳውዲ ድረስ በተወካዮቹ አማካኝነት መጥቶ ባናገረን መሰረት ነበር፤ ነገር ግን የተገባልን ቃል ታጥፏል” ይላሉ፡፡ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ባለመስጠቱ እና ለቤተሰብ መርዶ ባለመነገሩ፣ ለሚያውቋቸው ቤተሰቦች መርዶ ለመንገር ጭንቀት ላይ መሆናቸው ሌላ ችግራቸው እንደሆነ የተናገሩት ተመላሾች፤ አሁንም ቢሆን ሳውዲ ላይ ሃበሻዎችን በመኪና እየገጩ መግደል የሳውዲ ፖሊሶች የቀን ተቀን ስራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ታዲያ በዚህ አጣብቂኝ ውስጥ አምልጠው የሚመለሱ ዜጐችን ንብረት መቀማት ምን የሚሉት ተግባር እንደሆነ አልገባንም፤ በማለት አማርረዋል-ተመላሾቹ፡፡ ምናልባትም የፖለቲካ ማራመጃ ሊያደርጉን ነው በማለትም ስጋታቸውን አንፀባርቀዋል፡፡
ተመላሾቹ የተሟላ መጠለያ ተዘጋጅቶላችኋል በተባለበት ቦታ ሳይቀር፣ መተኛ ሥፍራ እንኳን እንዳልተዘጋጀ ሲረዱ ተስፋ መቁረጣቸውን እና ንብረታቸውን እንዳያስገቡ ሲከለከሉ፣ ተመልሰው በህገወጥ መንገድ ለመሰደድ ሙከራ መጀመራቸውን ይገልፃሉ፡፡ በጉዳዩ ላይ መልስ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በበኩላቸው፤ “ተመላሾቹ ስለንብረት የሚያነሱትን ጥያቄን በተመለከተ፤ እኛ ተመላሾች በሙሉ ንብረት እንደሌላቸው ነው የምናውቀው“ በማለት ተናግረዋል፡፡ አምባሳደሩ አልፎ አልፎ ባዶ እግራቸውን ከሳዑዲ የተመለሱ እንዳሉ ጠቁመው፤ በሳኡዲ መንግስት ጓዛችሁን ይዛችሁ እንዳትወጡ ተከልክላችኋል በመባላቸው፣ መጀመሪያውኑም ንብረት ይዘው ባለመምጣታቸው ነው፤ ብለዋል፡፡ እነዚህ ዜጎች ከመደበኛ የአየር መንገዱ ተጓዦች እኩል እንደማይስተናገዱና ለብቻቸው ተጠብቀው እንደሚስተናገዱ ገልፀው፤ ምናልባት ከነዚህ ዜጎች ጋር ተቀላቅለው የሚመጡ ሌሎች ሰዎች ስለሚኖሩ እሱን ለማጣራት ንብረታቸው ይፈተሻል እንጂ ማንም የእነሱን ንብረት የሚወስድ እንደሌለ የተናገሩት አምባሳደሩ፤ እንኳን በሀገር ውስጥ የገባ ንብረት፣ ሳዑዲ ያለውንም የላባቸውን ውጤት ለማስመጣት እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
የሟቾችን ቁጥር እና ለቤተሰቦቻቸው መርዶ አለመንገርን በተመለከተ አምባሳደሩ በሰጡት ምላሽ፣ አሁን ሙሉ በሙሉ ትኩረታችን በህይወት ያሉ፣ ንብረታቸውን ያጡ እና ጉዳት የደረሰባቸው ላይ ነው፤ ብለዋል፡፡ የሟቾቹን ቁጥር በተመለከተ ግን መንግስት ከገለፀው በኋላ፣ የተፈጠሩ ነገሮች መኖራቸውን አምነው፤ ነገር ግን ቁጥሩ ላይ ተመላሾች የሚሉትና አንዳንድ ሚዲያዎች የሚያወሩት ትክክል ሊሆን ቢችልም የተጣራ ነገር እስካላገኘን ድረስ የሞቱበትን ሁኔታ ለማወቅ ያስቸግራል፤ ብለዋል፡፡ የሳውዲ አየር መንገድ እንጂ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመመለሱ ሂደት ምንም አስተዋፅአ ለስደተኞቹ አላደረገም ለተባለው አምባሳደሩ መልስ ሲሰጡ፡- የሳውዲ አውሮፕላን የሚያመላልሰው እራሱ በማባረሩ ምክንያት ነው፤ ወጪውን የሚችለውም እራሱ ነው ብለዋል፡፡ addisadmas

Friday, December 6, 2013

በቦንጋ መምህራን አድማ ሊጠሩ ነው

esat

ህዳር (ሃያ ሰባ)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-በከፋ ዞን በቦንጋ ከተማ የሚገኙ መምህራን ፣ መንግስት ለአባይ ግድብ በማለት ያለፈቃዳቸው የቆረጠባቸውን ደሞዝ በአስቸኳይ ካልመለሰ ሰኞ የስራ ማቆም አድማ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።
መምህራኑ ዛሬ ወርሀዊ ደሞዛቸውን ለመቀበል ወደ ባንክ ሲሄዱ ለአባይ ግድብ በሚል ደሞዛቸው ተቆርጦ ተሰጥቷቸዋል። በሁኔታው የተበሳጩት መምህራን ወደ ትምህርት ጽህፈት ቤት ሲያመሩ መስተዳድሩ ያዘዘው በመሆኑ ምንም ማድረግ አንችልም የሚል መልስ ተሰጥቷቸዋል። መምህራኑም  አፋጣኝ መልስ የማይሰጠን ከሆነ፣ ከሰኞ ጀምሮ የስራ ማቆም አድማ እናደርጋለን በማለት ለመስተዳድሩ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
የመስተዳድሩ ባለስልጣናት በበኩላቸው፣ ውሳኔውን የሚቃወም መምህር ስራውን በራሱ ፈቃድ እንደለቀቀ ይቆጠራል በማለት የማስፈራሪያ ደብዳቤ ልከዋል።
ከዚህ ቀደም በጋሞጎፋ ዞን የሚገኙ መምህራን ተመሳሳይ ተቃውሞ በማሰማታቸው የተቆረጠባቸው ደሞዝ በፍጥነት እንዲመለስላቸው መደረጉን መዘገባችን ይታወሳል።

አሁን የውሸት ወይም ድራማዊ ለቅሶ ሳይሆን፤ የእውነት ሃዘን የምናይበት ጊዜ ይሆናል።

ኔልሰን ማንዴላ እና ኢትዮጵያ!!

December 6, 2013
የነጻነት ታጋዩ ኔልሰን ማንዴላ በ95 አመታቸው ከዚህ አለም ሲለዩ፤ የተለያዩ አገሮች እንደየራሳቸው ግንኙነት የራሳቸውን ታሪክ ሲያወሩ ነበር። የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ሃዘናቸውን ሲገልጹ ከማንዴላ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት በመግለጽ ነበር። እኔ በምኖርበት አትላንታ ከተማ ዜናው ሲቀርብ፤ ኔልሰን ማንዴላ አትላንታ በመጡበት ወቅት፣ ከነአንድርው ያንግ ጋር ሆነው የማርቲን ሉተር ኪንግ ማዕከልን ስለመጎብኘታቸው ነበር – ዋናው ዜና። ሁሉም አገር ስለማንዴላ የየራሱ ትዝታ አለው። ኢትዮጵያውያንም ስለኔልሰን ማንዴላ የራሳችን ታሪክ እና ትዝታ አለን። እናም ማንዴላ የዛሬ 51 አመት ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ስለነበረው ጉዳይ በማውጋት ታሪካችንን እንጀምራለን።
Nelson Mandela, the revered statesman who emerged from prison after 27 years
በዳዊት ከበደ ወየሳ
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር የነበሩት አቶ ከተማ ይፍሩ በ1962 ዓ.ም አራተኛው የፓን አፍሪካ ስብሰባ በኢትዮጵያ እንዲደረግ ጃንሆይን ፍቃድ ጠየቁ። ጃንሆይ በጉዳዩ ተስማሙና በፌብሩዋሪ 1962 ዓ.ም የአፍሪካ ታዋቂ የነፃነት ታጋዮች ወደ ኢትዮጵያ መጡ። ከእነዚህም መሃከል ሚስተር ኦሊቨር ታምቦ፣ ሚስተር ሮበርት ሙጋቤ፣ ሚስተር ኬኔት ካውንዳ እና ሚስተር ኔልሰን ማንዴላ ይገኙበታል። (በኋላ ላይ እነዚህ ወጣት ታጋዮች የየአገራቸው ፕሬዘዳንት ሆነዋል) ይህ ጉዞ በተለይ ለኔልሰን ማንዴላ በህይወታቸው ውስጥ ልዩ ስፍራ የሚሰጡት ነው።
Nelson Mandela and Col. Tadesse in Addis Ababa, Ethiopia
የኔልሰን ማንዴላ አሰልጣኝ ከነበሩት መካከል፣ ኮሎኔል ታደሰ አንዱ ነበሩ። ይህ ፎቶ ማንዴላ እና ኮ/ል ታደሰ (በሗላ ጄነራል) ለመታሰቢያ የተነሱት ነው
የኔልሰን ማንዴላን ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ያሰናዱት የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አቶ ከተማ ይፍሩ ነበሩ። በወቅቱ በአፓርታይድ የዘረኝነት ቀንበር ስር የነበረችው ደቡብ አፍሪካ ጥቁር ዜጎችዋ ያለፈቃድ አገሪቱን ለቀው እንዳይወጡ የሚያዝ ህግ አውጥታ ነበር። ይህ ህግ ለኔልሰን ማንዴላ ጉዞ አስቸጋሪ ሁኔታን ፈጠረ። በመሆኑም አቶ ከተማ ይፍሩ ለኔልሰን ማንዴላ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት መሆናቸውን የሚገልፅ ፓስ ፖርት ካዘጋጁላቸው በኋላ ነበር፤ በፌብሩዋሪ 1962 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ የመጡት። ማንዴላ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት፤ ወቅት ወታደራዊ ስልጠና ለማድረግ ነበር ወደ ኢትዮጵያ የመጡት።
በወቅቱ ለኔልሰን ማንዴላ የተዘጋጀው ፓስፖርት ላይ ማንዴላ እንደጋዜጠኛ ሆነው፤ ስማቸው ዴቪድ ሞሳማይ ተብሎ ነበር የተጻፈው። ስሙን የተጠቀሙት ደቡብ አፍሪካ እያሉ አብሯቸው ከነበረው ጓደኛቸው ነው።
ወደ ኢትዮጵያ ስለነበረው ጉዞ እናውጋ። ኔልሰን ማንዴላ “Long Walk To Freedom” በሚለው መፅሃፋቸው የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር አየር መንገድ ድረስ መጥተው እንዴት እንደተቀበሏቸው ገልፀዋል። እንዲህ በማለት ይቀጥላሉ ኔልሰን ማንዴላ…
ለንደን የነበሩትን ጓደኞቼን በወዳጅነት ስሜት ተሰናብቼ ወደ አዲስ አበባ- ኢትዮጵያ ተጓዝኩ። እስካሁን ባለው ህይወቴ ለማላውቀው ወታደራዊ ስልጠና ነው የምሄደው። የስድስት ወር ወታደራዊ ስልጠና ለማድረግ በያዝኩት ፕሮግራም መሰረት ነው ወደ ኢትዮጵያ የምጓዘው። አዲስ አበባ ስደርስ መጀመሪያ ተቀብለው ያነጋገሩኝ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ከተማ ይፍሩ ነበሩ። ሞቅ ያለ አቀባበል አደረጉልኝ። ከዚያም “ኮልፌ” ወደሚባለው አንድ የከተማው ክፍል ወሰዱኝ።
የኢትዮጵያ አድማ በታኝ ፖሊስ የሚሰለጥነው እዚህ ኮልፌ የሚባለው ሰፈር ነው። የባታሊዮኑ ዋና መስሪያ ቤት የሚገኘው ከዚህ ነው። አኔ ወታደራዊ የሳይንስ ጥበብ እንድማር የተመደብኩበትም ስፍራ እዚህ ነው። እስካሁን ባለኝ ልምድ ጀማሪ ቦክሰኛ ከመሆን ውጭ ስለጦር ሜዳ ፍልሚያ የረባ እውቀትም የለኝም። አሰልጣኜ መቶ አለቃ ወንድሙ በፍቃዱ ይባላል። በጣልያን ወረራ ግዜ የደፈጣ ተዋጊ የነበሩ ልምድ ያላቸው ወታደር ናቸው።
በአዲስ አበባ መውሰድ የጀመርነው የስልጠና ፕሮግራም ጥብቅ ነው። ከጠዋቱ 2፡00 ሰአት እስከ 7፡00 ሰዓት ድረስ ስልጠና ላይ እንቆያለን። ከዚያ የምሳ ሰዓት ነው። ከዚያ ከሰዓት ከ8፡00 እስከ 10፡00 ስልጠናው ይቀጥላል። ከ10፡00 ሰዓት በሁዋላ እስከምሽቱ ድረስ ስለ ወታደራዊ ሳይንስ የንድፈ ሃሳብ ገለጻ ይደረግልናል። ይህንን ስልጠና የሚያደርጉልን ኮሎኔል፤ የፖሊስ ረዳት ኮሚሽነር ናቸው። በንጉሱ ላይ የተደረገው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ እንዲከሽፍ ትልቅ አስተዋፅኦ አድርገዋል።
በስልጠናው የአውቶማቲክ መሳሪዎች እና የሽጉጥ አጠቃቀምን ተማርኩ።
መጀመሪያ ኮልፌ ከዚያም ከኮልፌ 50 ማይልስ የምትርቅ ቦታ ከወታደሮቹና ከንጉሱ የክብር ዘበኛ አባላት ጋር ሄጄ የኢላማ ተኩስ ተለማመድኩ። የሞርታር ተኩስና እንዲሁም የቦንንብ አሰራሮችን፤ ፈንጂዎችን የማክሸፍ ዘዴንም ተማርኩ። አሁን እያደር ወታደር እየሆንኩ ስሄድ ይታወቀኛል። እንደ ወታደር ማሰብ ለመድኩኝ። ወታደር መሆን እንደ ፖለቲከኛ ከማሰብ የሚለይበት የራሱ መንገድ አለው።
እዚህ ቦታ ላይ በጣም የወደድኩት ጠዋት ተነስተን የምናደርገው የማለዳ ጉዞ ነው። ጠመንጃ፣ ጥይትና ጥቂት ውሃ እንይዛለን። እናም በተሰጠህ ጊዜ ውስጥ ያንን ርቀት ተጉዘህ የታዘዝከውን ፈፅመህ መድረስ አለብህ። በዚህ ወታደራዊ ጉዞ የአገሪቱን ገጠራዊ ክፍሎች ለማየት እድሉን አገኘሁ። የመሬቱ አቀማመጥ በጣም ቆንጆ ነው። ጥቅጥቅ ያለ ደንና ከፍተኛ ቦታዎችን አየሁ። ገጠሩ በጣም ሁዋላ ቀር ነው። ሰዎች በእንጨት መቆፈሪያ ነው የሚያርሱት። ምግባቸውም ትንሽና በቀላሉ የሚዘጋጅ ነው። እቤት የሚጠመቅ ቢራ ወይም ጠላ አላቸው፤ ኑሯቸው እዚህ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ካሉ መከረኞች ጋር ተመሳሳይ ነው። መቼም ደሃ ሰዎች የትም ቢኖሩ ኑሯቸው አንድ አይነት ነው፤ ብዙም አይለያዩም።
በስልጠናዬ ወቅት ኮሎኔል ታደሰ ብዙ ጉዳዮችን እያነሱ ያስተዋውቁኛል። ስለ ደፈጣ ውጊያ፤ ሃይል እንዴት ማዋቀር እንደሚቻል አንድን ጦር እንዴት ማዘዝና መምራት እንደሚቻል፤ በጦር ውስጥ ወታደራዊ ስነ ስርአትን ለማስፈን ምን ማድረግ እንደሚገባ ያስተምሩኛል።
አንድ ምሽት እራት ላይ ለደቡብ አፍሪካ ትግል ምን አይነት ጦር እንደሚያስፈልገንና የሰራዊቱ ባህሪ ምን መሆን እንዳለበት አጫወቱኝ። “ይኸውልህ ማንዴላ… አንተ የምትመሰርተው ነፃ አውጪ ሃይል እንጂ መደበኛ ጦር አይደለም። የናንተን ጦር ሰዎች የምትቀርፅበት ስልት ከመደበኛው ጦር አሰራር የተለየ ነው። አንተ መመስረት ያለብህ ነፃ አውጪ ጦር ነው። በትግል ላይ ስትገባም የምትመራቸው ተከታዮችህ ፍፁም እርግጠኝነት እንዲሰማቸውና ሁሉም ሃሳብህን እንዲከታተሉ ማድረግ መቻል አለብህ። ይህ በመደበኛው ጦርም ውስጥ ያለ ነው። ከስራ በሁዋላ በእረፍት ሰዓትህ ማድረግ የሚገባህ ግን ከመደበኛው ደንብ ውጪ ይለያል። አንተና የመጨረሻው ተራ ተዋጊ እኩል መሆናችሁን የሚያሳይ አቀራረብ ሊኖርህ ይገባል። የሚበሉትን ትበላለህ፤ የሚጠጡትን ትጠጣለህ። ምግብህን ወደ ግል ክፍልህ መውሰድ የለብህም። እራስህን ገለል አታድርግ፤ እዚያው አብረሃቸው ሁን።” አሉኝ። የኮሎኔልን ሃሳብ ተረድቻለሁ። ሃሳቦቹ የሚደነቁና መልዕክት ያዘሉ ናቸው። እንደነዚህ ያሉ ቁም ነገሮችን በየፕሮግራሙ መሃል ይነግሩኝ ነበር።
ወደ አዲስ አበባ የመጣሁት ለስድስት ወር ስልጠና ነው። ስምንት ሳምንት እንደሆነኝ ግን ከድርጅቴ ‘የአፍሪካ ኮንግረስ’ አንድ የቴሌ ግራም መልዕክት ደረሰኝ። ባስቸኳይ ወደ ደቡብ አፍሪካ እንድመጣ የሚጠይቅ ነው። የዚያን ጊዜ የነፃነት ትግሉ መፋፋም ጀምሯል። እናም የግንባሩ አዘዥ እዚያው ቦታው ላይ መገኘት ስላለበት ነው የጠሩኝ። ኮሎኔል ታደሰ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ካርቱም የምሄድበትን መንገድ ቶሎ አዘጋጁልኝ። ስንሰነባበት አንድ ሽጉጥና ሁለት መቶ ጥይት ስጦታ አበረከቱልኝ። ስለ ስልጠናውም ሆነ ሰጡኝ ትምህርት ትልቅ አክብሮት እንዳለኝ ገለጽኩና ጉዞዬን ጀመርኩ። መሳሪያ ተሸክሞ ረዥም መንገድ መጓዝን ብለማመድም የተሰጠኝ መሳሪያ ከባድ ነው። ሁለት መቶ ጥይት ጀርባ ላይ መታጠቅ ህጻን ልጅ በጀርባ እንደማዘል ነው የሆነብኝ።
ኦገስት 5 ቀን፣ 1962 ላይ… ኔልሰን ማንዴላ ወደ ደቡብ አፍሪካ ኤርፖርት ሲደርሱ ጥብቅ ፍተሻ ተደረገባቸው። ከጦር መሳሪያው በተጨማሪ በኪሳቸውም ውስጥ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት መሆናቸውን የሚገልጽና የአቶ ከተማ ይፍሩ ፊርማ ያለበት ፓስፖርት ተገኘባቸው። በኢትዮጵያ መቆየታቸውን የሚገልጽ የጃንሆይ ማስታወሻና የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ከተማ ይፍሩ አነስተኛ ፎቶ ነበር። እነዚህን ጨምሮ 173 መረጃዎች በሪቮንያ የአፓርታይድ ችሎት ላይ ቀረበባቸው – 1963።
እነዚህና ሌሎች መረጃዎች በሪቮንያ ፍርድ ቤት ቀርቦ በኔልሰን ማንዴላ ላይ የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው፤ በዚሁ አመት በ1963 ሮቢን ደሴት ላይ ወደሚገኘው ወህኒ ተወረወሩ።
Nelson Mandela with Mengistu Haile Mariam
ኔልሰን ማንዴላ ከእስር ከተፈቱ በሗላ መጀመሪያ ኢትዮጵያን ሲጎበኙ በወቅቱ ፕ/ት መንግስቱ ሀይለማርያም አቀባበል ሲያድርጉላቸው
ከብዙ ውጣ ውረድና የ27 አመታት ትግል በኋላ ማንዴላ ከእስር ተፈቱ። እናም መጀመሪያ ከጎበኟቸው አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ነበረች። በፓስፖርታቸው ላይ ያሉት የመጀመሪያ ቪዛዎችም የሚያሳዩት ይህንኑ ነው። መጀመሪያ ከጎበኟቸው አገሮች መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ሆነች። በኋላ ላይ በመጽሃፋቸው ላይ ሲጽፉ፤ “ኢትዮጵያ በኔ ውስጥ ልዩ ስፍራ አላት። በፈረንሳይ፣ በእንግሊዝ እና በአሜሪካ ያደረኳቸው ጉብኝቶች ቢደመሩ እንኳን፤ በኢትዮጵያ ከነበረኝ ቆይታ አይበልጡም።” በማለት ለኢትዮጵያ ያላቸውን ልዩ ስሜት ገልጸዋል። (በነገርዎ ላይ የኔልሰን ማንዴላን የህይወት ታሪክ የሚገልጽ፤ በኢትዮጵያ ያሳለፉትንም ወታደራዊ ስልጠና ህይወት የሚያሳይ ትልቅ ፊልም ተሰርቷል)
ኔልሰን ማንዴላ ከ እስር ቤት ከወጡ በኋላ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ። በወቅቱ እነ ጄነራል ታደሰ ብሩ በህይወት አልነበሩም። ጊዜውም ተለውጧል። ቆየት ብሎ ኔልሰን ማንዴላ በህይወት ካገኟቸው ሰዎች መካከል አቶ ከተማ ይፍሩ አንዱ ነበሩ።
ከሰላሳ አመት በፊት አብረው የተነሱት ፎቶ ማንዴላን ለእስር እንዳላበቃቸው፤ አሁን ግን በነፃነት እንደገና ተገናኝተው የመታሰቢያ ፎቶ ለመነሳት በቁ። (አቶ ከተማ ይፍሩም ከጥቂት አመታት በፊት አልፈዋል)
ከመሰናበታችን በፊት… በአንድ ነገር እንሰነባበት። የኔልሰን ማንዴላ የልደት ቀን ሲመጣ፤ ተማሪዎችን ጨምሮ ህዝቡ በሙሉ ልደታቸውን ያከብራል። ለኔልሰን ማንዴላ ትልቁም ትንሹም “ማዲባ ሃላላ፣ እንወድሃለን አባባ” እያሉ ይዘምሩላቸዋል።
Madiba, Halala
Happy birthday to you!
Happy birthday to you!
Happy birthday dear Tata!
We love you Tata
We love you Tata
Nelson Mandela. Ha hona
Ya tshwanang le wena (there is no like you)
Yeep yeep!
Hooray!
እኛም በዚሁ ስንሰናበት፤ አንድ ነገር ለማለት ወደድን። አሁን የውሸት ወይም ድራማዊ ለቅሶ ሳይሆን፤ የእውነት ሃዘን የምናይበት ጊዜ ይሆናል።
ነፍስ ይማርልን!