Tuesday, August 19, 2014

የመከላከያ ሰራዊቱ ሊከዳ ይችላል በሚል ስጋት የወያኔ ጄኔራሎች ሲመክሩ ውለዋል።

ሻእቢያ ከከረን እና ከአስመራ ጦሩን ወደ ተሰንይ ማስፈሩን ተከትሎ ወያኔ ተጨማሪ ጦር ሲያጓጉዝ ዋለ።

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
የመከላከያ ሰራዊቱ ሊከዳ ይችላል በሚል ስጋት የወያኔ ጄኔራሎች ሲመክሩ ውለዋል።
ከሩሲያ ጋር የጦር ልምምድ ስምምነት እንዳደረገ የሚነገርለት የኤርትራ ገዥ ቡድን ሻእቢያ ከባለፉት ወራቶች ጀምሮ ጦሩን ወደ ደቡባዊ የኤርትራ ግዛቶቹ በመሰብሰብ ላይ መሆኑን ተከትሎ ወያኔም እንዲሁ ባለፈው ካሰፈረው ሰራዊት በተጨማሪ ከትላንትና ጀምሮ ከባድ የጦር ተሽከርካሪዎችን እና ተጨማሪ የጦር ሰራዊት በአከባቢው በማስፈር ላይ መሆኑ ታውቋል።
Ethio-army2 (1)
አሜሪካ እና ሩሲያ በአከባቢው ያላቸውን የበላይነት ለመቀዳጀት ፉክክር በገቡበት በዚህ ወቅት አከባቢው የጦርነት ቀጠና እንደሚሆን ቀድማ አሜሪካ በበረራ ደህንንነ ሰበብ ሹክ ባለችበት ሰአት እንዲሁም የሻእቢያ ተቃዋሚ ሃይሎችን ወያኔ በገንዘብ እና በቅስቁስ እየረዳ ባለበት ጊዜ በተጨማሪም በአግል ወያኔያዊ ትእቢት እየዛተ እንዳለ ሲሆን ለወያኔ ከፍተኛ ስጋት የሆኑበት ኢርታራ ውስት የመሸጉ ተቃዋሚ ሃይላት ስለሆኑበት በጭቆና የተምረረው ምከልከያ ሰራዊት ተቃዋሚዎችን ይቀላቅላል የሚል ከባድ ስጋት በሕወሓት ጄኔራሎች ላይ መከሰቱን ምንጮች ጠቁመውል።
ወያኔ በቅርቡ ከዩክሬይን ያስገባችቸን ቲ-72 ዘመናዊ ታንኮች በጦርነት ላይ ለማሰለፍ ወደ ሰሜን እያጓጓዘ ሲሆን ሻእቢያ በበኩሉ ሩሲያ ሰራሽ የሆኑ ዘመናዊ ታንኮች ሚሳኤሎች እና ከባባድ መሳሪያዎች፡ጸረ አይሮፕላን መድፎችን በአከባቢው አስፍሯል። ወያኔ ዘመናዊ መሳሪያ እና በታንክ ላይ የተጠመዱ መድፎችን ቢያምጣም በመክላከያ ሰራዊቱ ላይ ምንም አይነት መተማመን እንዳሌለው እየተናገረ ሲሆን በሰሜናዊ ትግራይ ብግብርና ሙያ ላይ ከነሙሉ ትጥቃቸው ያሰፈራቸውን የቀድሞ ታጋዮች እየቀሰቀሰ መሆኑ ሲታወቅ ህዝቡ ጦርነት እንደተሰላቸ እና ባለው ስርአት ላይ እምነት እንዳጣ በግልጽ እየተናገረ መሆኑ ታውቋል።

በሰራዊቱ ያልተማመነው ወያኔ አንድ የወሰደው እርምጃ ከሱዳን ጋር ያደረገውን የሰራዊት ቅልቅል ሲሆን ይህም ተቀላቅሎ መስራት በሰራዊቱ መኮንኖች ዘንድ ተቀባይነት አለማግኘቱ ታውቋል። የምዕራብ ኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለመስጠት ያሰበውን አገር የማጥፋት ሴራ ተግባራዊ ለማድረግ መሆኑን እና ሰራዊቱም ይህንን ተረድቶ ላገሩ ክብርና ታሪክ እንዲቆም ህዝቡ እየትናግረ ሲሆን የተደረገው የሰራዊት ውህደት ሱዳን በዳርፍርና ምስራቅ ሱዳን እንዲሁም ከደቡብ ሱዳን አቅጣጫ ላለበት ጦርነት በስምምነታቸው መሰረት የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲዋጉለት ለማድረግና ወያኔም በዚህ ጉዳይ ላይ መስማማቱን እናም በመከላከያ ሰራዊት ያለ የኢትዮጵያ ወጣት በጎረቤት አገሮች የበረሃ ሲሳይ ከመሆን ራስን እንዲታደግ አስተያየት ሰጪዎች አሳስበዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአዲስ አበባ የሚወጡ ዘገባዎች መጭውን የወያኔ የጦርነት ዝግጅት ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊቱ በመክዳት ከተቃዋሚ ሃይሎች ጋር ሊቀላቀል ይሽላል በሚል ስጋት ስብሰባ ተቀምጠው መዋላችውን ምንጮች ጠቁመዋል። በኤርትራ የሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ ሃይሎች የሚያወጡት መግለጫ በሰራዊቱ ላይ የሚፈጸመው ዘረኝነት እንዲሁም ብዝበዛ እና ከሃገሪቱ ጥቅሞች አንጻር እየተደረገ ያለው ብሄራዊ ውርድት በእጅጉ አሳሳቢ ደረጅ ልይ መድረሱ ሕዝቡ ለስር አቱ ያለው ጥላቻ መበራከቱ እንዲሁም ከዚህ ቀደም በባድመ ጉዳይ የተፈጸሙ መንግስታዊ ማጭበርበሮች እና የመሳሰሉት ግኡዳዮች ሰራዊቱ ይከዳል የሚል ከባድ ስጋት ያላቸው መሆኑን ያወሱት ጄኔራሎቹ በመከላከያ ሰራዊቱ ላይ እምነት በማጣትቸው ትግራይ ያለው የሕወሓት ታጣቂ ሃይል ከጀርባ እንደ ደጀን እንደ መተማመኛ እንደሚወስዱት መክረዋል።
ሰራዊቱ ያለውን ስርአት በተመለከት ደስተኛ ስላልሆነ እንዲሁም ሕዝቡ የሚፈልገው ለውጥ እንጂ ጦርንት ስላልሆነ ወያኔ በመጭው ሊያደርገው ያሰበው ጦርነት ከባድ ኪሳራ ያስክትልበታል ተብሎ ተገምቷል።

ወጣት ጥላዬ ታረቀኝ ዛሬ ፍድር ቀርቦ የዋስትና መብቱ ሳይጠበቅ ለዓርብ ቢቀጠርም የትግርኛ ሙዚቃ ለምን ተከፈተ ብሎ በሰው ላይ ጉዳት አድርሷል በሚል 2ኛ የክስ መዝገብ ተከፍቶበታል፡፡


ፍኖተ ነፃነት

10606390_684528351632102_6265250781347686507_n
በ4/12/06 እሁድ ማታ በደህንነት ኃይሎች በቁጥጥር ስር የዋለውና በእስር ላይ የሚገኘው ወጣት ጥላዬ ታረቀኝ በዛሬው እለት ፍርድ ቤት ቢቀርብም ፖሊስ ከሳሹን ስላላገኘሁትና የህክምና ማስረጃውን ስላልደረሰልኝ የጊዜ ቀጠሮ ይፈቀድልኝ ያለ ቢሆንም ወጣት ጥላዬ መርማሪው የምርመራ ስራን እየሰራ አይደለም ይልቁንም ራሱ ቢሮ የያዙኝ ደህንነቶች እየመጡ መርማሪው ባለበት ከእኛ ጋር ለመስራት ፈቃደኛ እስካልሆንክና የምንሰጥህን ተልዕኮ እስካልፈፀምክ እዚህ ትበሰብሳለህ እንጂ አትወጣም እያሉ እንደሚዝቱበት ለፍርድ ቤቱ ቢያስረዳም ፍ/ቤቱ ፖሊስ ለ16/12/2006 ፖሊስ መረጃዎቹን አጠናቆ እንዲያቀርብ እስከዛ የዋስና መብቱ ተቀባይነት አለማግኘቱን ብይን ሰጥቷል፡፡

ወደ እስር ቤት ሊሄድ በሚዘጋጅበት በድጋሚ ተጠርቶ 2ኛ የክስ መዝገብ እንደተከፈበት እና ክሱም በ12/10/2006 ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ላይ የትግርኛ ሙዚቃ እንዴት ይከፈታል በማለት በሰላም የሚዝናኑ ግለሰቦች ላይ ጉዳት አድርሶ ተሰውሯል የሚል ሲሆን ስለቀቀረበበት ክስ የተጠየቀው ጥላዬ እኔ ከአካባቢዬ አልተሰወርኩም ሲይዙኝም ከቤቴ በር ላይ ነው እስከዚህ ሰዓትም አላመሽም ፖሊስ እያቀረበ ያለው ክስ ከሳሽ በሌለበት ራሱ እየፈጠረ መሆኑን ፍርድ ቤቱ እንዲረዳልኝ እና የአንድነት ፓርቲ አባል በመሆኔ ባለኝ የፖለቲካ አመለካከት ጫና ለማሳደር የተወጠነ ውጥን መሆኑን መርማሪው ራሳቸው ያውቃሉ በማለት አስረድቷል ፡፡

ፖሊስ ለምን ጉዳት የደረሰበትን ግለሰብ እንዳላቀረበና 2ወር ሙሉ ፖሊስ የት ነበራችሁ ብሎ ፍ/ቤቱ ቢጠየቅም ከሳሽ ለጊዜው እዚህ ስለሌለና ልናገኘው ባለመቻላችን የህክምና ማስረጃውን እንድናቀርብ ይፈቀድልን በማለቱ ፍርድ ቤቱ የፖሊስን ማስረጃ ለመመልከት በ2ኛው ክስ ለ14/12/2006 ዓ.ም ለ3፡00 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ፖለስ እስካሁን በጥላዬ ላይ ክስ የመሰረተውን ከሳሽን ሊያቀርብ ካለመቻሉም ባሻገር ፍ/ቤቱን የህክምና ማስረጃ እንዳቀርብ ይፈቀድልኝ ማለቱ አግራሞትን ጭሯል፡፡

Monday, August 18, 2014

የወያኔው ኢንሳ በአዲስ መልክ የፌስቡክ ስም አጥፊ ፔጆችን/ገጾችን ሊያደራጅ ነው።

ነቢል አህመድ ዘገፈርሳ


 ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት እና ነጻነት ለመሸራረፍ ብሎም ለመበታተን ከሚጠቀምባቸው ዘዴዎች አንዱ በማህበራዊ ድህረገጹ ያሰማራቸውን ከተቃዋሚ ሃይላት ጋር ተመሳስለው የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት መስለው የተቃዋሚ ሃይሎችን ሎግ በመጠቀም እንዲሁም ለሽፋንነት በየመሃሉ የተቃዋሚ ድርጅቶችን መግለጫ እንደወሽመጥ በማስገባት በማታለል እና በማጭበርበር ላይ ተመስርተው ሲሰሩ የነበሩ ስም አጥፊ ገጾችን/ ፔጆችን በአዲስ መልክ ለማደራጀት በዚህ ሳምንት እረፍት እንዲወስዱ ያደረጋቸው መሆኑ ታውቋል።
 
ስም በማጥፋት ለውጥ ፈላጊ ሃይሎች በተለያዩ አክቲቪስቶች ላይ መጠራጠር እንዲያሳድሩ እና ጠቃሚ የተባሉ ጦማርያንን እንዲያጡ እና ትግሉ አቅጣጫውን እንዲስት በስፋት አዲስ የአሰራር ዘይቤ ለመቀየስ የተሳዳቢዎች የተዛልፊዎች እና የስም አጥፊዎች የማህበራዊ አካውንት እና ፔጆች እረፍት ላይ መሆናቸውን እና በተጠናከረ መልኩ ወደ ስራ እንደሚመለሱ በቅርብ የሚያውቋቸው ወዳጆቻቸው ተናግረዋል።
በዚሁም መሰረት በዜጎች መካከል ከባድ ጥርጣሬን ያጭራሉ የተባሉ የፈጠራ ጽሁፎች እና የሞቱ ሰዎች ፎቶዎችን በመጠቀም የተለያዩ የፌክ ወንጀሎችን በመጻፍ እንድሁም ከብልግና እና የሰውን ክብር ከሚያዋርዱ አዳዲስ ብካይ የሃሰት መረጃዎች ጋር ወዘተ ተያይዘው ወደ ማህበራዊ ድህረገጾች እርፍታቸውን ጨርሰው እንደሚመጡ ታውቋል።

Sunday, August 17, 2014

A must Watch Interview ESAT Bezih Samint Part 2


 ESAT Bezih Saminte with Tamagne Beyene, Ermias Legesse, Wendimagegne Gashu, August 10 2014, Part 2 | ESATTUB

ESAT Bezih Saminte with Tamagne Beyene, Ermias Legesse, Wendimagegne Gashu, August 10 2014, Part 2 

አንድ መንግስት እንደ መንግስት ከሚያሳዩት ነገሮች አንዱ በህዝቡ ላይ ስጋት የሚሆኑ ነገሮች እንዳይከሰቱ መከላከል ነው።

የኢትዮጵያ መንግስት ኢቦላን ለምን ፈለገው…!?


የኢትዮጵያ መንግስት ኢቦላን ለምን ፈለገው…!
ትላንት እነ ዮሃንስ ሞላ (ዮሃንስ ሞላ የብርሃን ልክፍት መድብል አሰናጅ ነው) እነርሱ የሚቀኙላትን ቅዳሜን የመሰለች ቀን ራሴን ክፉኛ ታምሜ አሳለፍኳት። ከመዕራብ አፍሪካ የመጣ ሰው ጋር ባለመገናኘቴ እንጂ የትኩሳቴ ነገር በሌላ የሚያስጠረጥር ነበር። (ሌላ የተባለው ኢቦላ ነው… ደጋግሞ በመጥራት ራሱ ይመጣብን ይሆን እንዴ እያልን ተሳቀን ሞትን እኮ ጃል…!
ከትላንት በስቲያ አይደል እንዴ… አየር መንገዳችን ከዩንጋንዳ ካምፓላ የመጣ አንድ ሰውዬ የበዛ ትኩሳት ታይቶበታል ብሎ ለኢቦላ መመርመሪያ ጣቢያ በተዘጋጀ ልዩ ስርፋ አስገብቶ የበዛ ምርመራ ሲያደረግለት ያየነው…!
እኔ የምለው እንዲህ ምልክት የሚመስል ነገር ሲታይ አፋጣኝ ምርመራ ማድረጉ ባልከፋ… ነገር ግን አየር መንገዳችን እስካሁንም ድረስ በመጨባበጥ ሁላ የሚተላለፈው አደገኛ ቫይረስ ወደተቀሰቀሰብት ምዕራብ አፍሪካ በረራ ማድረጉ ምኑን ተማምኖ ነው.. እንደሆነ ለምን አይነገረንም…!
በርካታ ሀገሮች፤ ለዛው በህክምናውም በመከላከሉም ዋዛ ያልሆኑቱ፤ ወደ ምዕራብ አፍሪካ ድርሽ አንልም ብለው ሲታቀቡ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ድርስ ምልስ፣ ድርስ ምልስ… እያለ እንደ ውሃ ቀጂ ሲመላልስ ብናይ የምርም ”የኢትዮጵያ መንግስት ኢቦላን ለምን ፈለገው…!” ብለን እየተጨነቅን እንገኛለን። መንግስት ኢቦላን አልፈለገውም ብሎ የሚሞግተን አካል ቢመጣ እንኳ ቢያንስ ነገር ሲፈልገው እያየን ነው ብለን እማኝነታችንን መስጠታችን አይቀሬ ነው…
እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ነገር ከገባ በቀላሉ አይወጣም። እንኳንስ ኢቦላ ይቀርና ኢህአዴግም እንኳ አልወጣ ብሎናል… (ልል ነበር ”ጽንፈኛ ዲያስፖራ ተቃዋሚ…” እንዳልባል ብዬ ትቼዋለሁ…) እውነቱን ለመናገር ግን አንድ መንግስት እንደ መንግስት ከሚያሳዩት ነገሮች አንዱ በህዝቡ ላይ ስጋት የሚሆኑ ነገሮች እንዳይከሰቱ መከላከል ነው። ሆን ብሎ በክፉ ልቦና ተነሳስቶ፤ አልያም ደግሞ በድንገት እና በነዋይ ፍቅር ተሳስቶ ህዝቡን ለስጋት የሚዳርግ ከሆነ መንግስት ሳይሆን መቅሰፍት ነው ብለን ከመደምደም ወደኋላ አንልም።
እናም አየር መንገዳችን፤ በበኩሌ ሳልናገር ብዬ እንዳይጸጽተኝ፤ ይሄ ኢቦላ የተባለ ክፉ ደዌ ወደ ሀገር ቤት ቢገባ ካንተ ራስ አንወርድም እና ካሁኑ ወደ አደገኛ ሀገሮች ከመብረር ክንፍህን ሰብስብ ለማለት እወዳለሁ!
 ከአቤ ቶክቻው

Saturday, August 16, 2014

በሰማያዊ ፓርቲ የአርባ ምንጭ አስተባባሪዎች የተጀመረው እስር ተጠናቅሮ ቀጥሏል ፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ እንደዘገበው፦

blue party
ከአሁን ቀደም አራት የሰማያዊ ፓርቲ የአርባ ምንጭ አስተባባሪዎች በሽብርተኝነት ስም መታሰራቸው ይታወቃል፡፡ እነዚህን እስረኞች ያሉበትን ሁኔታና የዞኑን አደረጃጀት ለመጎብኘት ከአዲስ አበባ (ከማዕከል) የድርጅት ጉዳይ ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድና የድርጅት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆነው ዮናስ ከድር ለጉብኝት በሄዱበት ወቅት ሲያስተባብሩ የነበሩት አባላት ከማዕከል የሄዱት የፓርቲው አመራሮች ሲመለሱ ለእስር መዳረጋቸውን ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ይጠቁማል፡፡

በመሆኑም አቶ ከሳሁን አየለ የተባለው የሰማያዊ ፓርቲ አርባምንጭ አስተባባሪ ከአዲስ አበባ የመጡትን የፓርቲው አመራሮች ጋር በመሆን የዞኑን አደረጃጀትና በእስር ላይ ያሉትን የፓርቲው አስተባባሪዎች አስጎብኝቷል በሚል መታሰራቸው ታውቋል፡፡ በተመሳሳይ ሻምበል ካሳ የታሰሩትን ጠይቀሃል በሚል ለእስር መዳረጋቸውንና ነፃነት የተባለው የፓርቲው አስተባባሪ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር እንዳይሰራና በታሰሩት ላይ እንዲመሰክር በማስፈራሪያ መለቀቁ ታውቋል፡፡
በዞኑ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እስራትና መከባ እየደረሰባቸው ሲሆን በአሁኑ ወቅትም ሉሉ መሰለ፣ በፈቃዱ አበበ፣ ካሳሁን አየለ፣ ሻምበል ካሰና ኢ/ር ጌታሁን የተባሉት የፓርቲው አስተባባሪዎችና አባላት በእስር ላይ እንደሚገኙ ለመረዳት ተችሏል።

Thursday, August 14, 2014

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የአፍ ወለምታ ።

ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰው የዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የአፍ ወለምታ ስለሙስሊም ታሳሪዎች – የጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ ልዩ ትንታ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ቴዎድሮስ ስለሙስሊም ታሳሪዎች ምን አሉ ? ድንበር የለሹ የህወሃት ፕሮፖጋንዳ ሲፈተሸ የዶ.ር ቴዎድሮስን ንግግር አስመልክቶ ሳዲቅ አህመድ ልዩ ዝግጅት አሰናድቷል

ሳዲቅ እዉነታዎችን በመፈተሽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ንግግር የ አፍ ወለምታ ሳይሆን ሚኒስቴሩ ሆን ብለዉ የፈጠሩት ብዥታ በመሆኑ ኦፊሴላዊ መግለጫ ሊሰጡ ይገባል ሲል ይደመድማልና ፕሮግራሙን እንከታተለዉ።

Wednesday, August 13, 2014

የሮዝ አሳታሚ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ እንዳልካቸው ተስፋዬን ፣ ኢብራሃም ሻፊ፣ እንዳለ ተሺና ሀብታሙ ሥዩም ከአገር መሰደዳቸውን ተሰማ፡፡

የአዲስ ጉዳይ መጽሔት አዘጋጆች ከአገር መሰደዳቸው

-ዓቃቤ ሕግ ክስ ሊመሠርት ነው
10570542_10204024912521089_4618968976545930065_n 
በሮዝ አሳታሚ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር አማካይነት ከኅዳር 1999 ዓ.ም. ጀምሮ ሲታተም የቆየው ‹አዲስ ጉዳይ› መጽሔት አዘጋጆች ከአገር መሰደዳቸው ተሰማ፡፡
የተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች የአዲስ ጉዳይ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተርና የሮዝ አሳታሚ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ እንዳልካቸው ተስፋዬን ጨምሮ የመጽሔቱ ምክትል ዋና አዘጋጅ ኢብራሃም ሻፊ፣ ከፍተኛ አዘጋጅ እንዳለ ተሺና የመጽሔቱ ዓምደኛ ሀብታሙ ሥዩም ከአገር መሰደዳቸውን ዘግበዋል፡፡
በቅርቡ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድና ሕዝቡ በመንግሥት ላይ ያላግባብ አመኔታ እንዲያጣ አድርገዋል በማለት የፍትሕ ሚኒስቴር ክስ እንደሚመሠረትባቸው ካስታወቀው አምስት መጽሔቶችና አንድ ጋዜጣ መካከል አዲስ ጉዳይ መጽሔትም መካተቱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የፍትሕ ሚኒስቴር መግለጫ የመንግሥትን ቻይነትና ትዕግሥት ከመጤፍ ባለመቁጠር የሚፈጽሙትን የሕግ ጥሰት አባብሰው በመቀጠላቸው፣ የአገሪቱ ሕግ በሚደነግገው መሠረት የወንጀል ክስ መመሥረቱን አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በታኅሳስ ወር 2006 ዓ.ም. ‹‹ሰባት መጽሔቶች በተከታታይ ሕትመቶቻቸው በአሉታና በተደጋጋሚ ያነሷቸው ጉዳዮች የአዝማሚያ ትንተና›› በሚል ርዕስ፣ በተመረጡ መጽሔቶች ላይ ከመስከረም 1 ቀን 2006 ዓ.ም. እስከ ኅዳር 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ድረስ ያሉ ሕትመቶች ላይ የዳሰሳ ጥናት አድርገው የጥናቱን ዋና ዋና ግኝቶች አውጥተው ነበር፡፡
በወቅቱ በወጣው ጥናት ዋና ዋና ግኝቶች መካከል የመንግሥትን ኃላፊዎችን የግል ሰብዕና የሚነኩ፣ የአመፃ ጥሪዎችን የሚጠሩ፣ የኢኮኖሚ ዕድገቱን የሚክዱና ሕገ መንግሥትን የሚያጣጥሉ ጽሑፎችን ማተም የሚል ሲሆን፣ አዲስ ጉዳይ መጽሔትም ከተዘረዘሩት የጥናቱ ግኝቶች በርከት ያሉትን አስተናግዷል፡፡ በማለት የአዝማሚያ ጥናቱን ገልጾ ነበር፡፡
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን የሕትመት ሚዲያዎች የሰኔ ወር 2006 ዓ.ም. አማካይ የኅትመት ሚዲያዎች ብዛት በድረ ገጹ ላይ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ በዚህም መሠረት አዲስ ጉዳይ 11,750 ኮፒ ማሰራጨቱን ይገልጻል፡፡ ከመጽሔቱ ባልደረቦች የመረጃውን ትክክለኝነት ለማጣራት ተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም የሞባይል ስልካቸው ዝግ በመሆኑ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ ፍትሕ ሚኒስቴር እከሳቸዋለሁ ባላቸው አምስት መጽሔቶችና አንድ ጋዜጣ ላይ ነሐሴ 7 ቀን 2006 ዓ.ም.፣ ዓቃቤ ሕግ ክስ እንደሚመሠርት ለማወቅ ተችሏል፡፡

Tuesday, August 12, 2014

በነኡስታዝ በድሩ ሁሴን ላይ የተፈጸመውን ግፍ ”በአፓርታይድ ጊዜ እንኳን ያልተፈጸመ” በማለት ዳኛው መኮነናቸው ታወቀ ‪



news
(ቢቢኤን ራድዮ) የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች በዛሬው እለት ፍርድ ቤት የቀረቡ ቢሆንም ዳኞች አልተሟሉም በሚል ያልተካሄደ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ለሁለቱ ዳኞች ግን እየደረሰባቸው ያለውን ነገር አህመድ ሙስጠፋና ኡስታዝ በድሩ ሁሴን በዝርዝር ማስረዳታቸው ታዉቐል፡፡ ቁልፍ ባለው ሰንሰለት በጨለማ ክፍል እንዳሰሩዋቸው ምግብም እንደከለከሏቸው የገለጹ ሲሆን ዳኛውም ይህን ሲሰሙ እንዴት እንደዚህ ይደረጋል በዚህ ዘመን ቀርቶ በአፓርታይድ ጊዜ እንኳን አይፈጸምም ነበር በማለት መኮነናቸው ታዉቐል፡፡ ዳኛውም አያይዘው እንኳን በ21ኛው ክፍለ ዘመን ቀርቶ አስርቱ ትእዛዛት በሚፈጸሙበት ጊዜ እንኳን እንዲህ አይነት ነገሮች አይደረጉም ነበር ማለታቸው ታዉቋል፡፡
ኮሚቴዎቹም አሰቃቂ ስቃይ በሚፈጸምበት በማእከላዊ እንኳን የምግብ ክልከላ እንደማይፈጸምባቸው ተናግረዋል፡፡ ኡስታዝ በድሩ ሁሴን የታሰረበት ሰንሰለት ረዥም ጥልፍልፍ ሲሆን ዙርያ ጥምም በማሰር ቆልፈውበት እንደነበር ገልጾ ካቴናውም የተፈታለት ፍርድ ቤት ሊመጣ ሲል ከ85 ሰአታት እስር በሁላ እንደሆነ ገልጽዋል፡፡
ጠዋት ወደ ፍርድ ቤት ሊመጡ ሲሉ ኮሚቴዎቹ የበድሩ ሰንሰለት ሳይፈታ ይሂድ ለፍርድ ቤት ማሳየት እንፈልጋለን ብለው የነበረ ቢሆንም የማረሚያ ቤቱ ሃላፊ በግዳጅ ሰንሰለቱን ፈተው ወደ ፍርድ ቤት እንዲሄድ እንዳደረጉ ለመረዳት ተችሏል።

Monday, August 11, 2014

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን መያዝ ተከትሎ ለወያኔዎች ከአዲስ አበባ እስከ ደብረዘይት ትልቁን የምርመራ ስራ እየሸፈኑ ያሉ ሶስት ከሃዲዎች ታወቁ

የከዱ የግንቦት 7 አባላት አቶ አንዳርጋቸውን እያሰቃዩ ነው ተባለ፤ * 2 መምህራንና 1 ዳኛ በአንዳርጋቸው ጉዳይ ታፍነዋ

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን መያዝ ተከትሎ ለወያኔዎች ከአዲስ አበባ እስከ ደብረዘይት ትልቁን የምርመራ ስራ እየሸፈኑ ያሉት ከግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ሃይል ጋር በኤርትራ የነበሩ እና ከአቶ አንዳርጋቸው ጋር የፖለቲካ ስራ ሲሰሩ የነበሩ በኋላም ከድተው የገቡ ቅጥረኞች መሆናቸው ታውቋል። እነዚህ ቅጥረኞች ከመጀመሪያው ሰርጎ ገቦች እንደሆኑ ሳይጠረጠር ወደ ግንቦት ሰባት ከገቡ በኋላ ከአቶ አንዳርጋቸው መያዝ ቀደም ብሎ በመክዳት ወደ ወያኔ የተቀላቀሉ ናቸው ሲል ጦማሪ ምኒልክ ሳልሳዊ ዘገበ።
Andargachew Tsigeእንደ ምኒልክ ዘገባ ከሆነ በአዲስ አበባ እና በደብረዘይት ትልልቅ ሆቴሎች ተይዞላቸው በምርጥ መኪኖች እየተንሸራሸሩ አቶ አንዳርጋቸውን በማሰቃያ ክፍል ውስጥ በማምጣት እውነቱን አውጣ አንተ እንደዚህ ብለኸን አልነበረም በማለት በተለያየ ጊዜ በስብሰባ እና በውይይት ወቅት የተነጋገሩትን የፖለቲካ ኦፕሬሽኖችን እና የትግል ስትራቴጂዎችን በመጥቀስ ከፍተኛ ስቃይ እና ድብደባ እያደረሱብት ነው።
ከሕወሃት ከአንድ ብሄር ከተመለመሉ መርማሪዎች ጋር በጋራ በምርመራ ላይ የተሰማሩት ሶስቱ የግንቦት ሰባት ከሃዲ አባላት አንዳርጋቸውን በማሰቃየት ላይ ያሉት -
1) ሽታው ሽፈራው ኤርትራ የነበረ የጎጃም ሰው
2) ቴዎድሮስ ስዩም ኤርትራ የነበረ ከአዲስ አበባ የሄደ
3) ኢልያስ ጥረት ጎንደር ውስጥ የነበረ እና ከአንዳርጋቸው ጋር ሲሰራ የነበረ ናቸው ሲል በዝርዝር የጠቆመው ጦማሪ ምኒልክ ሳልሳዊ በወያኔ ተንኮል ተተብትበው ግንቦት ሰባትን በመክዳት ለምቾታቸው የሕዝብን ትግል በጥቅም በመለወጥ በዘመናዊ መኪና እየተንፈላሰሱ በአዲስ አበባ እና ደብረዘይት ምርጥ ሆቴሎች ውስጥ እየተዝናኑ የነጻነት ታጋይ የሆነውን አንዳርጋቸውን በቶርች በማሰቃየት ላይ መሆናቸውን ዘግቧል።
ምርመርውን በመሪነት የሚያንቀሳቅሱት የሕወሓት ደህንነቶች የሆኑ የትግራይ ተወላጆች ሲሆኑ በአከባቤው አንዳርጋቸውን በተመለከተ ለብአዴን ይሁን ለ ኦሕዴድ ሰዎች ምንም አይነት መረጃ እንዳይሰጣቸውና ወደ ማሰቃያ ክፍሉ ምንም እንዳይቀርቡ ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገ እንደሆነ ለማረጋገጥ መቻሉን የገለጸው ጦማሪው ከአንዳርጋቸው ጋር የተያያዘውን የሃገር ውስጥ ኔትወርክ በማፈራረስ ረገድ ከላይ ስማቸው የተጠቀሰው ከሃዲዎች እስከ ክፍለሃገር ድረስ በስፋት እየሰሩ ሲሆን እስካሁን በማፈራረስ ሙከራው ምንም አይነት ውጤት እንዳልገኙ ታውቋል ብሏል።
ጦማሪው ዘገባውን ሲቋጭም “ከአንዳርጋቸው ጋር በተያያዘ ከየክልሉ የግንቦት ሰባት መዋቅር ውስጥ አሉ የተባሉ እየተለቀሙ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ከጎንደር ክፍለሃገር መምህር ተስፋዬ ተፈሪ እና መምህር ጌታቸው የተባሉ የሁለተኛ ደረጃ መምህራን እንዲሁም የጎንደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ እንደሆነ የሚነግረው አቶ አበራ በከሃዲዎች ጥቆማ ከሃምሌ አጋማሽ ጀምሮ ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ የት እንደታሰሩ እንኳን እንደማይታወቅ ተገልጿል።” ብሏል።

Saturday, August 9, 2014

ዴሴሶን ራዲዮ የነሃሴ 3 2006 ዝግጅታችን



program-poster-augest-09
እንደምን ስነበታችሁ የራዲዮ ዝግጅታችን ታዳሚዎች የነሃሴ 3 2006 ዝግጅታችን ያስተምራሉ ያዝናናሉ ያልናችውን ዝግጅቶች አጠናቅረን ይዘንላችሁ ቀርበናል ። በዜና የሚከፍተው ዝግጅታችን አየር አልባ ምድር በሚለው ዝግጅቱ ሪያድ ኢብራሂል ” ህዝባችን ብሶቱን ፣ ጭቆናውን፣ መበደሉን ፣መገፋቱን ፣ መናቁን ፣ ለማሰማት ሆነ ለመስማት አየር እንደሚያስፈልገው ሃቅ ነው ።አየር ደግሞ በኢሃዴግ እጅ ያለ ህዝቡ እንዳይሞት እንዳይሽር በራሽን የሚሰጥ እንክብል ሆኗል ።ሀገራችን በአሁኑ ሰአት እንደፓልቶክ ማይክ እየተነጠቀ ካልሆነ በስተቀር መናገር ክልክል የሆነበት ሀገር ሆናለች” ይለናል በማስከተልም የዳስሳ ዝግጅታችን አንጋፋው ጋዜጠኞ እስክንድር ነጋ ስራዎች ውስጥ ስለ አለማቀፍ ህዝባዊ አመጸ እንቅስቃሴዎችንና ውጤታችውን በአጭሩ ያቀረበውን ጸሁፍ ወቅታዊነቱን ተረድተን ለዚሁ ዝግጅታችን መርጠን አቅርበንላችኋል። በዝግጅቶቻችን እንደምትደስቱ በማስብ እንድታደምጡን እንጋብዛለን ።
 http://www.dceson.no/news/2014/08/09/5636/

Friday, August 8, 2014

የአማራ ክልል አመራሮች ከግንቦት7 የኦህዴድ ደግሞ ከኦነግ ጋር እያበሩ ነው

ሲል አቶ አዲሱ ለገሰ ያዘጋጁትና ለጠ/ሚ አማካሪዎች የተላከው ሰነድ አመለከተ

ethsat

ነሃሴ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰነዱ ላይ ኢህአዴግ የአመራር ችግር እንዳጋጠመው፣ የትራንስፎርሜሽኑ እቅድ አለመሳካቱ እንዲሁም በጋምቤላ ተማኝ መሪ መጥፋቱ ተዝርዝሯል።
በሃምሌ ወር መጨረሻ የተዘጋጀው ሰነድ ግልባጭ ለጠ/ሚኒስትሩ አማካሪዎች ለአቶ በረከት ስምኦን፣ ለአቶ ደስታውና ለአቶ ኩማ ደመቅሳ ተደርጓል።
የቀድሞው ም/ል ጠቅላይ ሚኒስትርና የኢህአዴግ የፖሊሲ ስልጠና ክፍል ሃላፊ የሆኑት አቶ አዲሱ ለገሰ ” የኢህአዴግን ተቃዋሚ ሃይላት ማንኮላሻ አቅም ግንባታ እና የአመራር ግንባታና የትራንስፎርሜሽን ጉዞ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ የፖሊሲ አማካሪዎች የቀረበ የሚለው ባለ 39 ገጽ ጽሁፍ፣ ኢህአዴግ ከላይ እስከታች የአመራር ችግር እንደገጠመው በዝርዝር ያቀርባል።

ጽሁፉ በመግቢያው “አገራችንን በፈጣን ቀጣይነት ያለውና ህዝቡ በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበት የእድገት ጉዞ ከድህነት አላቆ በተራዘመ ሂደት ከበለጸጉት አገሮች ጎራ ለማሰለፍ ይህንን ለማድረግ የሚያስችል አላማ፣ ስትራቴጂ ስልቶችና ፖሊሲዎችን መቀየስ ይጠይቃል። በሌላ አነጋገር አቅጣጫውን በትክክል የሚያመላክት መስመር መቀየስ የትራንሰፎርሜሽን ስኬት የመጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ነው።
መስመሩን ለመቀየስ ይህንኑ ማድረግ የሚችል ብቃት ያለው አመራር ይጠይቃል። ኢህአዴግ በዚህ ፈተና ውስጥ ነው።” ብሎአል።
ሰነዱ ” ለአብነትም እነ አቶ መላኩ ፈንታን ማንሳት ይበቃል” ይልና ” ይህን ተከትሎ በአገሪቱ ያሉ አመራሮች ለመቀበል አለመቻላቸው እና የኡመድ ኡቦንግ ሃገር መክዳት፣ በጋምቤላ ክልል ያለው አመራር ታማኝና አስተማማኝ አለመሆኑ፣ የአማራ ክልል አመራሮች ከግንቦት ሰባት ጋር የተያያዘ አመራር መገኘት፣ የኦህዴድ አመራር ከኦነግ ጋር በማበር እና በአማራ ላይ የደረሰውን በደል በቸልታ መመልከት” በማለት ይጠቅስና “በአሁኑ ሰአት በትግራይ ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ( የአመራሩ ቸልተኝነት እንደተጠበቀ ሆኖ)፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በሃረሬ ምርጫውን ማሸነፍ የሚችል አመራር ድምጽ የማግኘት እድል አለው” ብአሎል።
 
ሰነዱ “የትራንስፎርሜሽን ትግል በውል ይጀመራል እንጅ አይጠናቀቅም ቢባልም በስጋት በተቀመጡት ክልሎች አሁንም አፋጣኝ ስራ ካልተሰራ ኪሳራ ሊያመጡ ይችላሉ” ብሎአል። የአመራሩ ደካማነት የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ሳይሳካ እንዲቀር አድርጎታል የሚለው ሰነዱ፣ ድርጅቱ ሰዎችን የሚመለምልበትና የሚያሰለጥንበት መንገድም ብዙ ችግሮች ያሉበት በመሆኑ፣ የምልመላ ዘዴውንና የስልጠና መንገዱን እንዲቀይር ይመክራል።
 
ኢህአዴግን በመሰረቱ አራቱ ድርጅቶች መካከል ያለው ትውውቅ ደካማ በመሆኑ ከከፍተኛ እስከ መካከለኛ አመራር ያሉት በአንድ ማእከል ስልጠና እንዲሰጣቸው እየተደረገ መሆኑንም
ተጠቅሷል። ኢህአዴግ እጅግ በጣም የሚበዛው አባሉ አርሶ አደር በመሆኑ ፣ የፖለቲካ መሪዎችን በብዛት ለመፍጠር አለመቻሉን የሚጠቅሰው ሰነዱ፣ ከእንግዲህ በዩኒቨርስቲዎችና በከተሞች ላይ ትኩረት ተደርጎ ሰዎችን የመፈለጉ ስራ እንዲጀመር ያሳስባል።

Thursday, August 7, 2014

ታዋቂው ፖለቲከኛና መምህር ወጣት አብርሃ ደስታ ዛሬ ፍ/ቤት ቀርቦ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀበት

Abrha Desta


በአራዳ መጀመሪያ ፍ/ቤት ችሎት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ይቀርባል ቢባልም ዘግይቶ 10 ሰዓት ከ25 ላይ ቀርቧል፡፡ ፖሊስ ሀምሌ 3 ቀን ፍ/ቤት ቀርቦ ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ በሽፋን ትሰራለህ በሚል በቁጥጥር ስር አድርጎ ለምርመራ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆበት የነበረ ሲሆን በ28 ቀን ውስጥም ምንም ማስረጃ ለችሎቱ አላቀረበም፡፡ በችሎቱ ላይ የአረና አመራር አቶ ካህሳይ፣የአብርሃ እህት በችሎቱ እንዲታደሙ ተፈቅዶላቸው ገብተዋል፡፡ አብርሃ ደስታ በእስርቤት የደረሰበትን ለችሎቱ ሲያስረዳ እያስገደዱ ቃል ተቀብለውኛል፣ ተደብድቤያለሁ፣ ከውጪ የመጡ የደህንነት ኃይሎች ምርመራ አድርገውብኛል፣ ጨለማ ቤት ለቀናቶች ነበርኩ፣ የማላውቀውንና ያላነበብኩትን እንደፈርም ተደርጌያለሁ፣ የጨጓራ በሽተኛ ሆኜ በግድ እንጀራ እንድበላ ተደርጌያለሁ በማለት ለፍ/ቤቱ አስረድቷል ፡፡

 ፖሊስ እነዚህ ድርጊቶች በፖሊስ ጣቢያው እንደማይደረጉና ማስረጃ የሌላቸው ውንጀላዎች ናቸው በማለት ያስተባበለ ሲሆን፣ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ደንበኛቸውን የሚመረምረውን መርማሪ ስም እንዲገለጽ ቢጠይቁም የመርማሪውን ስም አንናገርም ይዞ ፍ/ቤት የሚያቀርበውን ፖሊስ ስም ብቻ ነው የምንናገረው በማለት መልሰዋል፡፡ 
አቃቤ ህግ ለምርመራ ተጨማሪ የ28 ቀን ቀጠሮ ጠይቆ ፍ/ቤቱ የ28 ቀን ቀጠሮውን ፈቅዶ ለነሐሴ 29 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት እንዲቀርብ አዟል፡፡

 የፍርድ ቤቱን ሂደት ለመከታተል አረና፣ የአንድነት፣ የሰማያዊ፣ የመድረክ፣የጌዴኦ የፓርቲ አመራሮችና አባሎቻቸው፣ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች በርካታ ሰዎች ተገኝተው አብርሃ ወደ ፍ/ቤት ግቢ በሚገባበትና በሚወጣበት ጊዜ በጭብጨባና አይዞህ በማለት አጋርነታቸውን ሲገልጹ አብርሃ ደስታም አንገቱን ዝቅ በማድረግ የታሰሩ እጆቹን ከፍ በማድረግ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
ምንጭ፡-ፍኖተ ነጻነት

Wednesday, August 6, 2014

ስለኢቦላ በሽታ ማወቅ ያለብዎ 10 ነገሮች

 
 1. የኢቦላ በሽታ ምንድ ነው?
የኢቦላ በሽታ በቫይረስ ምክንያት የሚመጣ፣ በፍጥነት ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍና በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሞት የሚዳርግ በሽታ ነው፡፡ የኢቦላ በሽታ በምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በተደጋጋሚ በመከሰት ከፍተኛ ህመምና ሞት እያደረሰ የሚገኝ በሽታ ነዉ፡፡ በሽታው በማንኛውም ወቅት በአገራችንም በወረርሽኝ መልክ ሊከሰት የሚችል በመሆኑ ከወዲሁ ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ ይሆናል፡፡ የኢቦላ በሽታ ለከፍተኛ ህመምና ለሞት የሚዳርግ ቢሆንም መከላከል ግን ይቻላል፡፡
2. የኢቦላ በሽታ መተላለፊያ መንገዶች፡-
•በኢቦላ ከታመመ ሰው ቁስል፣ ደም፣ ምራቅ፣ ትውከት፣ አይነምድርና ሽንት ጋር በቀጥታ በመነካካት ወይም እነዚህ ፈሳሾች ወደ ጤነኛ ሰው አይን ከተረጩና ከገቡ፣
•ንጽህናቸው ባልተረጋገጠ ወይም ሌሎች ህሙማን የተጠቀሙበትን መርፌ ሳይቀቅሉ በመጠቀም፣
•የኢቦላ በሽታ ታማሚ የተጠቀመባቸዉን ስለታማ መሳሪያዎች በመጠቀም፣
•በኢቦላ በሽታ የሞተ ሰውን አስከሬን በቀጥታ በመነካካት፣
•በኢቦላ በሽታ የሞተውን እንሰሳ ስጋ በመመገብ ናቸው፡፡
3. በኢቦላ በሽታ የተያዘ ሰው የበሽታዉን ምልክቶች የሚያሳያው መቼ ነው?
በኢቦላ በሽታ ከተጠቃ ሰው ጋር ንኪኪ የፈጠረ ሰው ከ 2 እስከ 21 ቀናት ባለዉ ጊዜ ውስጥ የበሽታውን ምልክቶች ማሳየት ይጀምራል፡፡
4. በኢቦላ በሽታ የተያዘው ሰው የሚያሳያቸው ምልክቶችና ስሜቶች፡-
•ድንገተኛና ከፍተኛ የሆነ ትኩሳት ይይዘዋል፡፡ በተጨማሪም ማስመለስ/ትውከት/፣ ተቅማጥ፣ ራስ ምታት፣ የቆዳ ሽፍታ እና የአይን ቅላት ምልክቶች ይታዩበታል፡፡
•በሰውነታችን ክፍት ቦታዎች ማለትም አይን፣ አፍንጫ፣ ድድ፣ ጆሮ፣ ፊንጢጣና በብልት በኩል የመድማት ምልክት ሊታይም ላይታይም ይችላል፡፡
5. በኢቦላ በሽታ መያዙ የተጠረጠረ ወይም የተያዘ ሰው ከገጠመን ምን ማድረግ አለብን?
•ታማሚውን በምንረዳበት ጊዜ ሰውነታችንን ከበሽታው መከላከል የሚያስችለንን የእጅ ጓንት፣ የአይን መከላከያ መሳሪያ (ጎግል) እና የአፍንጫና የአፍ መሸፈኛ ማስክ መጠቀም፤
•የታመመውን ሰው ወድያውኑ ለአስፈላጊ ህክምናና እርዳታ በአቅራቢያው ወደሚገኘው ጤና ተቋም መወሰድ፤
•በኢቦላ በሽታ የተጠረጠረ ሰው በሚገኝበት ወቅት ወድያውኑ በአቅራቢያው ወደሚገኘው ጤና ተቋም ወይም ጤና ጽ/ቤት ሪፖርት ማድረግ፣
•በበሽታው መያዙ የተጠረጠረ ወይም የታመመ ሰው የተጠቀመባቸዉን አልባሳትና መኝታውን በበረኪና ማጠብ ይኖርብናል፡፡
6. ለኢቦላ በሽታ ተጋላጭ የሆኑት ማናቸው?
•በሽታዉ ከታመመ ሰው የሚወጣውን ደምና ሌሎች የሰውነት ፈሳሾች በቀጥታ በመነካካት የሚተላለፍ በመሆኑ ከታመመው ሰው ጋር የሚኖር ማንኛውም ሰው በበሽታዉ ሊያዝ ይችላል፡፡
•በሽተኛውን በሚመግቡበትና በሚንከባከቡበት ወቅት የእጅ ጓንትና ሌሎች መከላከያ መሰሪያዎች ሳያደርጉ ከሰውነት ፈሳሽ ጋር ንክኪ የሚፈፅሙ ሰዎች በቀላሉ በበሽታው ሊያዙ ይችላሉ፡፡
•በኢቦላ በሽታ የሞተውን ሰው አስከሬን ያለ እጅ ጓንትና ሌሎች የመከላከያ መሳሪያዎች የምንነካካ ከሆነ በቀላሉ በበሽታ ልንጠቃ እንችላለን፡፡
7. የኢቦላ በሽታን እንዴት ልንከላከል እንችላለን?
•የእጅ ጓንት፣ የአይን ጎግል እና ሌሎች የሰውነት መከላከያ መሳሪያዎችን በመጠቀም በበሽታው ከተጠቃ ሰው ውስጥ ከሚወጣው ማንኛውም ፈሳሽ ጋር በቀጥታ ባለመነካካት፤
•ያለ እጅ ጓንት በበሽታው የተጠቃውን ሰው ቁስል አለመንካት፤
•በኢቦላ በሽታ የተያዘው ሰው የተጠቀመውን መርፌና ሌሎች ስለት ያለቸውን መሳሪያዎች አለመጠቀም፤
•በኢቦላ በሽታ መያዙ የተጠረጠረና የሞተ እንስሳን ሥጋ አለመመገብ፤
•በኢቦላ በሽታ የሞተን ሰው አስከሬን ያለጓንትና ሌሎች የመከላከያ መሰሪያዎች ያለመንካት፣ የቀብር ሥነ ሥርኣቱም በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈፀም ማድረግ ፤ እንዲሁም ከቀብር በኋላ ያለውን ስነስርዓት ማሳጠር፤
•የታመመውን ሰው ከረዳን ወይም በበሽታዉ ምክንያት የሞተውን ሰው አስከሬን ከነካን በኋላ እጃችንን በውሃና በሳሙና በደንብ መታጠብ፣
8. በቤት ውስጥ መወሰድ ያለበት ጥንቃቄ ፡-
•በኢቦላ በሽታ የተጠቃ ወይም የተጠረጠረ ሰውን በተቻለ መጠን ለብቻው በተዘጋጀ ቦታ መለየት፣
•በበሽታው የተጠቃ ወይም የተጠረጠረን ሰው ወደ ጤና ተቋማት በምንወሰወድበት ወቅት ከታማሚው ጋር አላስፈላጊ ንክኪ አለማድረግ፣
•በበሽታው ከተጠቃ ወይም ከተጠረጠረ ሰው ወይም የሰውነት ፈሳሽ ጋር ንክኪ ከተፈጠረ ወዲያውኑ እጃችንን በውሃና በሳሙና መታጠብ፣
•በኢቦላ በሽታ የተጠቃውን ሰው በምንረዳበት ወይም በምንንከባከብበት ወቅት የእጅ ጓንት፣ የአይን ጎግል፣ የፊት መሸፈኛ እና ሌሎች የሰውነት መከላከያ መሳሪያዎችን መጠቀም፣
•በበሽታው የተጠቃ ወይም የተጠረጠረ ሰው የሰውነት ፈሳሽ መሬት ከበከለ በረኪና ይጨምሩበት፤ ከ15 ደቂቃ በኋላም ይፀዳ፤ በቆሻሻ የተነካኩ ቁሳቁሶችና አልባሳት መቃጠል ይኖርባቸዋል፣
•በኢቦላ በሽታ ታሞ የሞተ ሰው የቀብር ስነስርዓት ሲፈፀም ከአስከሬን ጋር ንክኪ አለማድረግ፣ የጋራ እጅ መታጠቢያም አለመጠቀም፣
•የቀብር ስነስርዓት ሲፈፀም አስከሬኑ በፕላስቲክ ከረጢት መጠቅለል፣ የቀብር ስነስርዓት ሲፈፀም በሰለጠነ የጤና ባለሙያ ምክር መታገዝ፣
9. በሽታው ወደ ሀገራችን ሊገባ የሚችልባቸዉ ሁኔታዎች፡-
በሽታው እስከ አሁን በሀገራችን ያልታየ ቢሆንም በምዕራብ አፍሪካ ሀገሮችና በሀገራችን መካከል ባለው የህዝብ እንቅስቃሴ ምክንያት በማንኛውም ጊዜ ወደ አገራችን ሊገባ ይችላል፡፡ በተለይም በኤርፖርቶችና በድንበር አከባቢ ባሉ መውጫና መግቢያ በሮች በኩል ሊገባ የሚችልበት አጋጣሚ ሊፈጠር ስለሚችል አስፈላገው ጥንቃቄ መደረግ ይኖርበታል፡፡
10. እየተወሰዱ ያሉ እምጃዎች
በሽታው እስከ አሁን ወደ ሀገራችን ባይገባም ከወዲሁ ለመከላከልና ከተከሰተም አፋጠኝ ምላሽ መስጠት እንዲቻል በቂ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር በአየር መንገዱ የሚጓዙ መንገደኞችን ጤንነት ሁኔታ መለየት፣ የታመመ ሰው ከተገኘም ወዲያውኑ ህክምና የሚያገኝበት ሁኔታ ተመቻችቷል፡፡ እንዲሁም የህክምና ግብዓቶችና ለባለሙያዎች የሚሆን የመከላከያ መሳሪያዎች ተለይተው በመሟላት ላይ ይገኛሉ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ ጤና ተቋማት ለተውጣጡ የጤና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ውስጥ መስጠት ዝግጅት ተጠናቋል፡፡

ከአፍሪካ ጋር ባለው የንግድ ልውውጥ አሜሪካ መሪነቱን እንደያዘች ነው፡፡



 አፍሪካ ተለዋዋጭ በሆነው የአየር ንብረት ሁኔታ ውስጥ ቻይ ሆና እንድትዘልቅና በምግብ እራሷን እንድትችል አንድም ሌሎች በአፍሪካ ሊያምኑ እንደሚገባ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የአህጉሪቱን ቁርጠኝነት ወደተግባር ለመለወጥ የአሜሪካ ድጋፍ እንዲሰፋ ተጠይቋል፡፡
እነዚህ ሃሣቦች በተነሱበት በፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ጋባዥነትና አስተናጋጅነት በተካሄደው የአፍሪካ - ዩናይትድ ስቴትስ የመሪዎች ስብሰባ ላይ በተሰናዳው የአፍሪካ ተለማጭነት ወይም የተፈጥሮ አካባቢና የአየር ንብረት መለዋወጥ ቻይነትና የምግብ ዋስትና መድረክ ላይ መክሯል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ አፍሪካና ዩናይትድ ስቴትስ ተባብረው በመሥራታቸው በያዝነው የአውሮፓ ዓመት የውጭ መዋዕለ ነዋይ ፍሰቱ ሰማንያ ቢልዮን ዶላር መድረሱ ተገልጿል፡፡
በፍጥነት በማደግ ላይ የሚገኘውን የውጭ ኢንቭስትመንት የአሜሪካ ኩባንያዎች በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
በጉባዔው ላይ የተገኙት አፍሪካዊያኑ መሪዎች ከአፍሪካ የንግድ ድርጅቶች መሪዎችና ከዩናይትድ ስቴትስ ኩባንያዎች ጋር በምጣኔ ኃብቱ ዙሪያ መክረዋል፡፡

Tuesday, August 5, 2014

በሁለት ካርቶን ታሽጎ ወደ ዱባይ ሊወጣ ሲል የተያዘው ወርቅ በጄነራል ሳሞራ የኑስ ትዕዛዝ እንዲወጣ መደረጉ ተዘገበ።

samora and azeb

በሁለት ካርቶን ታሽጎ ወደ ዱባይ ሊወጣ ሲል የተያዘው ወርቅ በሳሞራ የኑስ ትዕዛዝ እንዲወጣ መደረጉን ምኒልክ ሳልሳዊ ዘገበ።
እንደዘገባው ከሆነ የጄኔራል ሳሞራ የኑስ እንደሆነ የሚጠረጠረው አንድ መቶ ሰባ አምስት ኪሎ ወርቅ ከአገር ሊወጣ ሲል ተይዞ የነበረ ቢሆንም በጄኔራሉ ትእዛዝ ከአገር እንዲወጣ መደረጉን የአየር መንገዱ የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል። ይህ በሁለት ካርቶን ታሽጎ በበረራ ቁጥር 600 እና 612 ወደ ዱባይ ሊሻገር ሲል በቁጥጥር ስር የዋለው ወርቅ በጊዜው ባለንብረቱ ተፈልገው ባለመገኘታቸው እንዲቆይ ቢደረግም ጄኔራል ሳሞራ የኑስ ቦታው ድረስ አሽከሮቹን በመላክ እንዲለቀቅ እና እንዲያልፍ/እንዲጫን የተደረገ መሆኑ ታውቋል።
ዘገባው ጨምሮም ይህ የሃገር ሃብት የሆነን ወርቅ የወያኔ ባለስልጣናት ካለምንም ገደብ በማሸሽ እና በመዝረፍ ላይ የተሰማሩ ሲሆን ፒያሳ አከባቢ በሚገኘው በአፍሪካ ወርቅ ቤት ሽፋን እንዳልካቸው እና ዳንኤል በሚባሉ ስሞች በሚሊዮን ዶላሮች የሚገመት የወርቅ መጠን ከአገር በማስወጣት እና እንዲሁም የውጪ ወርቆችን ካለምንም የቀረጥ ክፍያ ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት ስራ ላይ መሰማራታቸው በተጨማሪም ሃገሪቷ የምታገኛቸው የውጪ ምንዛሬዎች በጥሬው እየታሸጉ ከሃገር እንደሚወጡ ታውቋል ሲል ጠቁሟል።

በጅዳ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ካድሬዎች የአቶ በረከትን ገበና አጋለጣችሁ በሚል ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ሲያዋክቡ ዋሉ።

አዲስ መረጃ በአቶ በረከት ዙሪያ፡ ምስጢር አወጡ የተባሉትን የጂዳ ቆንስላ ጽ/ቤት እያመሰ ነው

ሰበር ዜና አቶ በረከት ስሞኦን ዛሬ August 5, 2014 የሆስፒታል ቀጠሮቸውን ያጠናቅቃሉ !
« በአቶ በረከት ጉዳይ ካድሬዎች ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤትን ሲያምሱ ዋሉ »

bereket alamudi demeke
ሳውዲ አረቢያ በህክምና ላይ የሚገኙት አቶ በረከት ስሞኦን ከህመማቸው አገግመው ሼክ አላሙዲን ወደ አዘጋጁላቸው ሚስጥራዊ ሆቴል ካቀኑ ወዲህ እኚህ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ስላሉበት የጤነነት ሁኔታ በእርግጠኝነት መናገር ባይቻለም ከሁለት ቀን በፊት የሼክ አላሙዲን ወደ አሜሪካ ማቅናት ተከትሎ የአቶ በረከት ስሞኦን የ ጤንነት ሁኔታ በመላካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ መረጃዎች ያመላክታሉ ። አቶ በረከት ስሞኦን እስካሁን ሳውዲ አረቢያ ከሚገኙ ዲፕሎማቶች ጋር በስልክም ሆነ በአካል እንዳለተጋናኙ የሚገልጹ እነዚህ ምንጮች እኚህ የመንግስት ከፍተኛው ባለስልጣን ያረፉበት ሆቴል ምሲጥራዊነቱ በከፍተኛ ጥንቃቄ የተጠበቀ መሆኑን ይናገራሉ።
 
የአቶ በረከት የጤንነት ሁኔታ በማህበራዊ ገጾች መነጋገሪያ ከሆነ ወዲህ ጭቀት ውስጥ የገቡት ሼክ አልሙዲን የተለያዩ ሆቴሎችን እየቀያየሩ እኚህን የመንግስት ባለስልጣን ደብቀው ሲያስታምሙ እና አሰፈላጊውን ድጋፍ ሲያደርጉላቸው መክረማቸውን ለማውቀ ተችሏል። አቶ በረከት ከሆስፒታል ከወጡ ወዲህ የተለያዩ ሆቴሎች እንዳረፉ የሚገልጹ መረጃዎች ሼኩ ወደ አሜሪካ ከማቅናታቸው በፊት በግል ከተከራዩላቸው ምርጥ ሆቴሎች ምናልባተም የመጨረሻ የአቶ በረከት ሚስጥራዊ ማገገሚያ ይሆናል ተብሎ ከሚነገርለት ሆቴል ነገ ወደ «ቡግሻን» hospital በማቅናት የመጭረሻ የህክምና ቀጠሮአቸውን ካጠናቀቁ በሃላ በአጭር ቀን ውስጥ፡ ወደ ሃገር ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተያያዘ ዜና በህክምና ላይ የምትገኘው የ6 አመቷ የአቶ በረከት ልጅ ህጻን ህሊና በረከት በመልካም ጤነት ላይ መሆኗን የኢትዮጵያ ሃገሬ የሆስፒታል ምንጮች አረጋግጠዋል ።

ይህ በዚህ እንዳለ በጅዳ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ካድሬዎች የአቶ በረከትን ገበና አጋለጣችሁ በሚል ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ዛሬ የመጡ ኢትዮጵያውያን ሲያዋኩቡ መዋላቸው በጅዳ እና አካባቢው ኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተናኛ ቁጣን ማስነሳቱ ን ለማረጋገጥ ተችሎል ። ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የተለያዩ ጉዳዮቹን ለማስፈፀም በጠራራ ጸሃይ ሲነፍሩ የነበሩ ኢትዮጵያዊያንን እንደ ዜጋ አዝነው በአግባቡ ከማስተናገድ ይልቅ አቶ በረከት መታመማቸውን መረጃ ያወጣችሁት እናንተ ናችሁ የተቃዋሚ ወሬ አቀባዩች እናተን ሰብስቦ ማቃጠል ነበር በሚል ዛቻ ፍጹም ኢትዮጵያዊ ነኝ ከሚል የድርጀት አባል በማይጠበቅ ቃላት በኢ.ህ.ዴ.ን ካድሬዎች እና የህወሃት ካድሬዎች ሲያዋክቡ ሲዋከቡ መዋላቸውን በደሉ የተፈፀመባቸው ወገኖች ገልፀውልናል። በተለይ እራሳቸውን ብቸኛ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ፈላጭ ቆራጭ አድርገው ያስቀመጡት የህወሃት የቀድሞ ታጋይ አቶ ገሬ እና መዝገብ ቤት ሃላፊ የሆነው የትግራይ ተወላጁ የቀድሞው የህወሃት ታጋይ አቶ ሽፋ ባለጉዳዮችን ሲያንገራግሩ ከነበሩ መሃከል ግንባር ቀደም እንደነበሩ ታውቋል።
የጅዳ ቆንስል ሃላፊ የነበሩትን ቆንስል ዘነበን በተጽዕኖ ያስነሱት እንዚህ የጅዳ ኢህአዴግ ካድሬዎች የጅዳን ቆንስላ ጽ/ቤት በመቆጣጠር ደካማ ዲፕሎማቶችን በመናቅ እንዳሻቸው በማድረግ ከማድረጋቸውም በላይ ለጉዳይ የመጣውን ኢትዮጵያዊ ማጉላላት እና ፓስፖርት እስከ መንጠቅ የደረሱ ወንጀለኞች መሆናቸው በአብዛኛው የጅዳ ማህበረሰብ ዘንድ ይነገራል። ከዚህ መሰሪ ተግባራቸው ያልታቀቡት እንዚህ ግለሰቦች የአቶ በረከትን ለህክምና መምጣትን መረጃ አወጣችሁ የሚሏቸውን ወገኖች ወደ ቆንስላው ግቢ ሲገቡ በመተናኮል ሁከት ቀሰቀሱ ብለው ለማሳሰር በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ከጽ/ቤት የወጡ መረጃዎቻችን ጠቁመዋል።

Monday, August 4, 2014

ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማሪያም ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራውን በስልጣን ጥመኝነት ከሰሱ!!

አንድነት ከቲፎዞ ነጻ የሆነ ምርጫና መሪ ያስፈልገዋል!!….hqdefault

በቅርቡ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ለመሆን በዕጩነት ቀዳሚ ሆነው ማለፋቸው የፓርቲው ልሳን የሆነው ፍኖተ ነጻነት አስታውቋል፡፡በዚህ ጉዳያ ያልተናደደና ያልተበሳጨ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ይኖራል ብሎ መገመት ይከብዳል፡፡ በተለይ ያእቆብ ሀ/ማሪያም በግንቦት 25/2005 በሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ ላይ በኩባ አደባባይ ለሰልፈኛው አቅርበውት በነበረው ንግግቸው ላይ “እኛ አባቶች ከእንግዲህ ሀላፊነት ለወጣቶች በመስጠት በምክርና የተለያየ ተሞክሯችን በመስጠት ከጎናቸው መቆም አለብን፣ከእንግዲህ የእኛ ሀላፊነት ወንበሩን ለወጣቱ ለአዲሱ ተውልድ መልቀቅ ነው፣ “ብለው ነበር፡፡ኢንጂነር ግዛቸው ግን እንዲህ ቅዱስ ነገር ለመስማት ፍላጎትም ያላቸው አይመስልም፡፡ኢህአዴግም የእሳቸው ወደ ፊት መምጣት እንደ ሰማይ መና የሚቆጥረው ነገር ነው፡፡ ለምን?

፣ሰውዬው ታሰረው ከነበሩትና በኋላም በይቅርታ ከተለቀቁት የቅንጅት አመራሮች አንዱ ነበሩ፡፡እና ምን አለበት ሊባል ይችላል፡፡በጣም ከባድ ችግር ነው ያለበት፡፡ዋናው ነገር ምን አይነት ይቅርታ ጠይቀው ነው የወጡት የሚለው ነው፣ እንዲህ የሚል ነው

….ህገ መንግስቱንና ህገመንግስታዊ ስርአቱን በሀይልና በአመጽ ለመናድ በህገወጥ መንገድ ተንቀሳሰናል በዚህም ምክንት ብዙ ጥፋትና ውድመት ተከስቷል፤እንዲህ አይነት ነገሩ ውስጥ በማድረግ ህዝባችንና መንገስታችንን በመበደላችን አጥፍተኛል ተጸጽተናል፣ከእንግዲህም አይለመደንም ይቅርታ ይደረግልን… የሚል አይነት ነበር፡፡


ኢህአዴግ በእንዲህ አይነት ሁኔታ ይቅርታ እንዲጠይቁ ያደረገው በትክክል የተባለው ነገር ስለፈጸሙ ሳይሆን፣፣ከእስር ትፈታላችሁ ነገር ግን ካሁን በኋላ እኔ ከምላችሁ አንዳች ፍንክች ብትሉ ተመልሳችሁ ትገቧታላችሁ ማለቱ እንደሆነ ትርጉሙ ግልጽነው፡፡ለዚህም የብርቱካን ሚደቅሳ ነገር ማየት ረዘም ተደርጋ እንዳተሰረች ዶሮ እንጂ እኝደወፍ እንድትበር አልተፈቀደላትም፡፡ስዊድን ሀገር ሄዳ ኢህአዴግ የማይፈቅደው ነገር ተናግራ ወደ ሀገር ቤት ስትመጣ ብዝብ ፊት ይቅርታ ጠይቂ አለበለዛ በተስማማስ መሰረት ወደነበርሽበት ትመለሻለሥ ጠባለች፡፡እምቢ አለች፡፡ተመለሰች፡፡በወቅቱ አብዛኛው የአንድነት አመራሮች በፊርማ የወጡ ስለነበሩ ለምን ብለው ሊከራከሩላት አልቻሉም፣እንዳውም የሚሉሽን አትሰሚምና የእጅሽን ነው ያገኘሽው በሚል አይነት ሁኔታ በብዙ መንገድ ሊኮንኗትና ሊያሳጧት ሞክረዋል፡፡

በወቅቱ ደግሞ ድርጅቱን በሀላፊነት ይመሩ የነበሩት ዛሬ ቲፎዞ አሰልፈው የመጡት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ነበሩ፡፡እኚህ ሰው በወቅቱ ብርቱካን የታሰረችው እስርቤት የገባችውን የፊርማውን ቃል ስላቃለለች ነው የሚል በሚመስል የብርቱካንን ስም የሚያነሳ ሁል በድንጋይ ሳይቀር እስከማስደብበብ ደርሰዋል ውሸታም የሚለኝ ያ አይመስለኝም፡፡ከድርጅቱ አግደዋል አባረዋል፡፡ለዚህም የዛሬዎቹ የሰማያዊ ፓርቲ መሪዎችና አባላትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ሰውዬው ድርጅቱን ይመሩት እስርቤት የፈረሙትንነገር በህልማቸውና በቅዠታቸው እየመጣባቸው ነበር፡፡ ለኢህአዴግ የገቡትን ቃል ለማክበር ብዙ የደርጅቱን ወጣቶችና ስም አባክነዋል፡፡ዘሬም ያ ፍርሀታቸው ደብቀው በፍርሀት ሊመሩት ከነቲፎዟቸው ብቅ ብለዋል፡፡በነገራችን ላይ ይህ ሰው በ97 ምርጫ ወቅት ፓርላማ እንግባ አንግባ በሚባልበት ወቅት እንግባ (ኢህአዴግ የሰጠንን ተቀብለን እንግባ) ብለው ይከራከሩ የነበሩ ከዚህም የሀገር ፍቅር ይኖራቸው ይሆናል እንጂ ወደፊት ገፍቶ ኢህአዴግን ለመታገል የሚጎላቸው ነገር እንዳለ ማወቅ ይቻላል፡፡ለጫማው በኋላ ይታሰብበታል ላሁኑ ማምለጥ ነው የሚሉ አይነት ሰው ናቸው፡፡


እና ምን ለማለት ነው ? ሰውዬ የአንድነት መሪ ቢሆኑ ድርጅቱን የሚመሩት ያኔ በፈረሙት ፊርማ ታስረውና ተሸብሽበው ነው፡፡አንዷል አተራጌ አፌን ሞልቼ ስለነጻነት አወራለሁ ሲል አትችል እንዲህ ማድረግ እንደማትችል እስርቤት ፈርመሀል ተብሎ ይኀው የትእንዳለ እናውቃለን፡፡ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ የፈረው ፊርማ በሀገር ቤት የትም እንደማያደርሰው አውቆ ይኸውየት እንዳለ እናውቃለን፣እዛም አልቀረለትም የሞት ፍርድ ተፈርዶበታል፡፡ዶ/ር ያእቆብ ቃሊቲ እያለሁ የፈረምኩት ፊርማ እያሰብኩኝ የኢትዮጵያን ህዝብ ትግል ከምጎዳ አርፌ ብቀመጥ ይሻላል ብለው ይመስላል ይኸው መሪ አይደለም የየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባልም አይደሉም፡፡ብርቱካንም በውሸት ታስራችሁ በተጭበረበረ መንገድ የፈረማችሁት ፊርማ እፈራችሁ የምትኖሩ ከሆነና ሌላውም ሲታሰር ፍርዳችሁና ና ምላሻችሁ ይሄ ከሆነ ብላ ሀገሩም ትግሉም ጥላ ተደብቃ እየኖረች ነው፡፡

ኢንጂነር ሀይሉሻውል መለስን ጎንበስ ብለው እጅ ነስቻለሁ ያሉት ወደው አይደለም፣ የፈረሙት ፊርማ ምን ያህል ቀልባቸውና ቅስማቸውን እንደሰበራቸው መገመት ይቻላል፡፡ያኔ ታስረው የነበሩ ጋዜጠኞች ሀገር ጥለው ያሉት ቃሊትን ብቻ ሳይሆን የፈረሙትንም ፊርማ ስለሚፈሩ ጭምር ነው፡፡ኢህአዴግ ሰማያዊ ፓርቲ በአደረጃጀትም ሆነ በዐጣቃላይ ጥንካሬ ከአንድነት ስለሚበልጠው አይደለም እንዲህ ልቡ የተሸበረው፣የቀሊቲን ፊርማ እያሰቡ የሚመሩ ሰዎች ስላልሆኑ ጭምር ነው፡፡

ስለዚህ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው የአንድት መሪ ሆኑ ማለት ድርግቱ ክንፍ ብቻ ያለው የማይበር የታሰረ ዶሮ ከመሆን ውጪ ምንም አያመጡም፡፡ ስለዚህ በገዛ ፈቃዳቸው በቃኝ ብለው ከጎን ሆነው የትግል ልዳምቸውና ምክርብቻ ማካፈል አለባቸው፡፡ ደግሞም ባለፈው 22 ውስጥ ፖለቲካ ውስጥ ብዙ ጊዜጣቸውን ያሳለፉት እንደ በየነ ጴጥሮስና ዶ/ር መራራ ጉዲና በድርጅት አመራርነት በተለያየ ቦታ ተለጥፈው ተጣብቀው ነው ነው፡፡ለኢህአዴግ የጣሉት እንጂ ያስጣሉት ነገር የለም፡፡ሸክም መሆን ብቻ፡፡መአድ ውስጥ አመራር ውስጥ ነበሩ፣መኢአድ ውስጥ እንዲሁ፣ቅንጅት ውስጥ የታሰሩት አመራር ላይ ስለነበሩ ነው፣አንድነት እሰካሁን የሚያሳማውን ስም ያሰጡትም አመራር ላይ ስለነበሩ ነው፡፡አይተናቸዋል ፣በቃ አሁን ቦታውን ለሌላ ይልቀቁ!!በተለይ የእሳቸው ወደ ስልጣን መምጣት ድርጅቱን እንደእነ ቡልቻ ባሉ “የበራላቸው” ሰዎች በብሄር (በተለይ መዐአድ ውስጥ የነበሩ ሰው ከመሆናቸው አንጻር)በጣም የሚያሳማና ኢህዴግም የያኔው አንዳንድ የቅንጅት ስህተቶችን እያነሳ ህዝብ የሚያስትበት አጀንዳ ናየትግል መግደያ ከመሆን አያልፉም!!

ኃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች አሜሪካ ከመግባታቸው በፊት የኢቦላ ቫይረስ እንደሚመረመሩ ተገለጸ

 ሰሜን አሜሪካ ከነገ ጀምሮ በሚደረገው ትልቅ ስብሰባ ላይ የሚሳተፉ ኃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ የአፍሪካ መሪዎች ስብሰባው ውስጥ ከመግባታቸው አስቀድሞ ከኢቦላ ቫይረስ ነፃ መሆናቸውን ምርመራ እንደሚያደርጉ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ አስታወቁ።

Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn speaks during an interview with Reuters inside his office in the capital Addis Ababa
ከ729 ሰዎች በላይን የገደለውና በርካቶችን በቫይረሱ ተጠቂ ያደረገው ኢቦላ በአሁኑ ወቅት የታማሚዎች ቁጥር ከ 1 ሺህ 200 በላይ እንደሚሆንና ቫይረሱም ከአገራቱ አልፎ በስፋት በመሰራጨት የአህጉሪቷ ብሎም የዓለም ስጋት ሊሆን እንደሚችል ባለሙያዎች የሰጡትን አስተያየት በመጥቀስ ሲኤን ኤን መዘገቡ አይዘነጋም።
በጊኒ፣ በሴራሊዮን እና ላይቤሪያ በርካቶችን እየፈጀ ያለውና የአፍሪካም ትልቁ ስጋት እንደሆነ የሚነገርለት ይኸው በሽታ ወደ ስሜን አሜሪካ እንዳይሰራጭ መንግስታቸው በሰፊው እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወቁት ባራክ ኦባማ ይህ ለ3 ቀናት በዋሽንግተን ዲሲ የሚደረገው በዚህ ትልቅ ስብሰባ ላይ ከ50 በላይ የአፍሪካ መሪዎች የሚገኙ ሲሆን ሁሉም የኢቦላ ምርመራ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

ይህ ሰሚት (ስብሰባ) ነገ ኦገስት 4 ተከፍቶ ኦገስት 6 ቀን 2014 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሲዲሲ የተባለው የአሜሪካ የጤና ተቋም ባለፈው ሰኞ በሰጠው መግለጫ፣ በአገሪቱ ይህ ነው የሚባል የኢቦላ ወረርሽኝ ስጋት እንደሌለ አረጋግጧል፡፡ ይህም ሆኖ ግን በሽታው አደገኛ በመሆኑ መጠንቀቅ ይበጃል ብሏል ተቋሙ፡፡ በሽታው ከተከሰተባቸው የአፍሪካ አገራት የሚመጡ መንገደኞችን ወደ አሜሪካ አለማስገባት ሁነኛ መከላከያ መላ ነው ይላሉ- የሲዲሲ ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት ዶ/ር ማርቲ ሴትሮን፡፡ በቅርቡ ከእነዚያ አገራት የመጡና የኢቦላ ምልክቶች የተሰሟቸው ሰዎችም፣ ዛሬ ነገ ሳይሉ በአፋጣኝ ወደ ህክምና መሄድ እንደሚኖርባቸው ዶክተሩ መክረዋል፡፡ በአገራቱ የሚኖሩ ዜጎችም፣ የበሽታውን መተላለፊያ መንገዶች ጠንቅቀው በመረዳት ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተናግረዋል፡፡
  • 532
     
    EmailShare
(ዘ-ሐበሻ)

Saturday, August 2, 2014

በዋሽንግተን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሊኢ ህ አ ዴ ግ ባለስልጣናት አንመችም አሉ..


non_pulsating_econ_caption

ይቺ አባባል ራሷ ቀላል ተመቸችኝ እንዴ፤ ትላንት በዋሽንግተን ዲሲ በአንዱ ምግብ ቤት ደረታቸውን ነፍተው ሊበሉ ሊጠጡ ተከስተው የነበሩት የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔ አንዳች ጫን ያለ ነገር ገጥሟቸው፤ ሳይበሉ ሳይጠጡ ጎንበስ ብለው እንደወጡ ተሰማ፤
ባለስልጣኑ የገጠማቸው ነገር ሳይወዱ በግዳቸው ልክ ልካቸውን መስማት ሲሆን፤ ይህንን ያደረጉ የዲሲ ወጣቶች የ ኢ ህ አ ዴ ግ ባለስልጣናት በተገኙበት ቦታ ሁሉ፤ በህዝብ ምግብ ቤትም ይሁን በህዝብ መጽዳጃ ቦታ እየጠበቁ ልክ ልካቸውን መንገር እና የሁላችንም ሃላፊነት ነው ሲሉ ይናገራሉ።
ይህንን ማድረግ ፋይዳው ምንድነው… ሲል እሳት የላሰው የኢሳት ጋዜጠኛ መሳይ ከበደ በጠየቃቸው ጊዜም፤ ”እነርሱ በኢትዮጵያ ላሉ ወንድሞቻችን አልመች እንዳሉ ሁሉ እኛም እንርሱን ምቾት መንሳት ዋናው አላማችን ነው” ሲሉ መልሰውለታል።
የኢ ህ አ ዴ ግ ባለስልጣናት ባለፈው ጊዜ በአቶ መልስ ላይ የደረሰውን ነገር ረስተውታል መሰለኝ ሰኞ በአሜሪካ ዋሽንግተን ለአንዳች ስብሰባ ልዑካን ልከዋል አሉ። ዘንድሮ ደግሞ ማን ደንግጦ ሊሞት ይሆን እያልን እየተጨነቅን ባለበት በዚህ ሰዓት የዲሲ ወጣቶች ለባልስልጣኖቹ ኮረኮንች መንገድ ሆነው አልመች ብለዋቸዋል። (ባለስልጣኖቹም ምን አለኝ ኮብል ስቶኔ… እያሉ መስሪያ ቤታቸውን እና መሳሪያ ታጣቂዎቻቸውን እየናፈቁ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው)
በዚህ አጋጣሚ ሰኞ በዋሽንግተን እና አካባቢዋ ይሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለስልጣኖቹ ላይ የተቃውሞ ቁጣቸውን ለማሰማት ተቀጣጥረዋል። ባለስልጣኖቻችን እንግዲህ ቆፍጠን ነው! ብለን እንምከር ወይስ ይቻሉት…! ?